ሀገራዊ ሁኔታ በፖለቲካ ለውጥ ዋዜማ
ኢትዮጵያ ወደ ፌዴራሊዝም ስርአት የገባችበት መንገድ ድንገተኛ የሚባል አይደለም”” በተለይም በመጀመሪያ የአብዮቱ አመታት ሀገር አቀፍ ፖለቲካ ፓርቲዎች ከጨዋታ ውጪ መሆን ፀረ
ወታደራዊ የደርግ መንግስት የሚካሄደው ወታደራዊና ፖለቲካዊ ትንቅንቅ በዋናነት በብሄራዊ መልክ በተደራጁ ድርጅቶች የሚመራ ሆነ፡፡
በሰሜን፣ በምዕራብ፣ በደቡብና በምስራቅ የሀገሪቱ ክፍሎች የተነሱ ታጣቂ ሃይሎችም ደርግን
በማዳከም የነበራቸው ሚና ተመሳሳይ ባይሆንም እነዚህ ድርጅቶች የህዝቡን ብሄራዊ ማንነትና ንቃተ ህሊና ማዳበር ላይ ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል፡፡
በሁለቱም ምክንያት ከደርግ በኋላ የምትኖረው ኢትዮጵያ ፌዴራላዊ አወቃቀር ያላት፣ በፌዴራላዊ አወቃቀሯም ለብሄር ብሄረሰቦች ያልተሸራረፈ
ፖለቲካዊ መብትና ስልጣን የሰጠች መሆን እንዳለባት አመላከች ነበር፡፡ ዞሮ ዞሮ ግን በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ አጀንዳ ለ17 አመታት
በየዘርፉ የቀጠለ ነበር፡፡ ኢህአዴግ አምባገነን የደርግ መንግስት ስርአት በማስወገድ ብቻ ሳይሆን ሕብረብሄር ፌዴራላዊት ስርአትን
በማዋለድ ግንባር ቀደም ሚና ተጫውቷል፡፡
1983 ወርሃ ግንቦት ለብዙዎች የመጨረሻ ጥይት የተተኮሰባት የጦርነት መክተሚያ ትሆን ዘንድ
ለብዙዎች ምኞት ሲሆን ብሶት ለወለዳቸው ታጋዮቹ ደግሞ እምነት ነበር”” ቁጥራቸው
ቀላል ያለሆኑ ወገኖች ደግሞ የአስከፊ ጦርነት ማክተሚያ ሳይሆን መጀመሪያ ይሆናል የሚል ግምገማ፣ እምነትና ‹‹ተስፋ››ም ጭምር
ነበር፡፡ የኢትዮጵያም እጣ ፈንታ እንደ ዩጎዝላቪያ፣ ላይበሪያና ሶማሊያ ሊሆን ይችላል የሚል ግምገማ የነበረው የአለም አቀፍ ማህበረሰብ
ደርግ መውደቁ ባይቀርለትም ቢያንስ ቁርሾውን ለማስቀነስና ጠባሳውን ለመሻር በራሱ መንገድ እያበቃለት የነበረው ጦርነት በሰሙ እንዳይጠናቀቅ
ብዙ ተሯሩጠዋል፡፡ ይሁን እንጂ እንዳሰቡት አልሆነም፡፡ በጦርነት የጀመረው የኢትዮጵያ አብዮት በጦርነት ተቋጨ፡፡
ኢህxÁG
rጅÑን õRnT yGD bõRnT mÌÅ lþÃgŸ YgÆL y¸L xÌM xLnbrWM”” bxþHxÁG XÂ xÆL
DRJècÜ xStúsB õRnT y±ltEμ x§¥ ¥úkþà xND x¥‰ጭ yTGL SLT XN©þ ‰sùN yÒl HLW XNdl¤lW bsnìcÜ
btdUU¸ xINåT s_è XÂgßêlN”” l¤§ qRè yxþT×eà HZïCንyzmÂT _Ãq½ lmmlS XSμSÒl DrS dRG xþsፓፓy¸útFbT y>GGR mNGST XSkmmSrT y¸ÿD x¥‰ጭ XNd¸qbL yxlM ¥HbrsB b¸ÃWqW አኳኋን bYÍ nbR ÃwjW”” lxBnT HwˆT mUbþT 1981 ÆμÿdW 3¾ DRJ¬êE gùÆx¤ ÆwÈW Æl xMST n_B ys§M
¦úB YHNN bGLI xSFé¬L”” bzþH BÒ úYwsN khùlT wR bº§M ldRG mNGST bGNïT 1981 wR YÍ
dBÄb¤ Éf”” YHNNM bbwQtÜ bÊDዮW lHZB bYÍ xS¬WÌL”” dRG GN lHwˆT/xþHxÁG _¶
b¯ M§> xLs«M””
YH
XNÄÃdRG ÃdrgW bxND bkùLÂ bênŸnT lDRJtÜ YÍêE XWQÂ mSጠ«T nW k¸L ÄtŸnT
nW”” bl¤§ bkùL GN bwQtÜ ÆLtgmt hùn¤¬ ÷lÖn¤lù bjn‰lÖÒcW ymfNQl mNGST Ñk‰
SltdrgÆcW bb¤¬cW s§M mrUUT bm_ÍtÜ b² gùÄY Slt«mÇ YçÂL”” bmNGStÜ XMbþtŸnTM
bþÃNS q_lW btμÿÇT yhùlT xm¬T ጦርነትbhùltÜM wgN Bzù xSR ¹þãC HYwትተቀጠፈ፡፡
በዚህ አጋጣሚ አንድ ፖለቲካዊ ፋይዳ ያለው የኢሀአዴግ ውሳኔ ልጥቀስ፡፡ ጀነራሎቹ ያልተሳካ መፈንቅለ መንግስት ባደረጉበት
ቀን ሻዕቢያ ለመፈንቅለ መንግስቱ ድጋፍና እውቅና ሲሰጥ ኢህአዴግ ግን በጥርጣሬ ነበር የተመለከተው”” ጀነራሎችም ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጥሪ አድረገውለት ነበር፡፡ ኢህአዴግ ግን መፈንቅለ መንግስቱ
ነገሮችን ከማወሳሰብ ባለፈ የኢትዮጵያ ህዝቦች የዘመናት የስልጣን ጥያቄ በመመለስ ረገድ ፋይዳ እንደሌለውም በግልፅ አስታወቀ፡፡
ኢህአዴግ አንድ ምክረ ሀሳብም ሰጣቸው፡፡ መኮንኖቹ በሃሳባቸው ከቀጠሉበት ቢያንስ መላው ሰራዊቱ ማሳተፈ እንዳለባቸው ካልሆነ ግን
በስርዓቱ የበላይ መደብ የሚደረግ የአመራር ሽግሽግ ሌላ ደርግ እንጂ ሌላ ለውጥ እንደማያመጣ አፅንኦት ሰጥቶ ህዝባዊ አቋሙን ግልፅ
አደረገላቸው፡፡
በወቅቱ ደርግ ጎንደርና ሰሜን ወሎ የነበሩትን የኢህአዴግ ሰራዊት ለመጨፍለቅ ዝግጅት ላይ እንደነበርም ኢህአዴግ እውቀቱ
ነበረው፡፡ ኮሎኔሉም ወንበራቸውን ባረጋጉ ማግስት ሰኔ 3/1981 ጎንደር በሃሙሲት ከተማ ላይ በገበያ ቀን በሚግ የጦር አውሮፕላን
በፈፀመው ድብደባ 105 ሰዎችን በመጨፍጨፍ ለኢህአዴግ ምላሽ ሲሰጡ ከሻዕቢያ ጋር ግን የሰላም ድርድር እንደሚደረጉ አስታወቁ፡፡
ወታደራዊ መንግስት የሰላም አፈላላጊ ለመምሰልና ሰላም ፈላጊነቱ የአውሮጳ መንግስታት ይቀበሉት ዘንድ በርካታ ዲፕሎማቶቹን
ወዲያ ላከ፡፡ ነገር ግን የልኡካኑ መሪ የነበሩ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ ብርሃኑ ባይህ ከጋዜጠኞች ባደረጉት ቃለመይቅ የሰላም ውይይት
ለማድረግ የተዘጋጀው ከሻዕቢያ ብቻ መሆኑ አስረግጠው ተናገሩ፡፡ ስለሆነም ያወጣው ባለ ስድስት ነጥብ የሰላም ሃሳብ ህውሓትና ኢህዴን
በተናጠል ወይም አዲስ የመሰረቱት ግንባር/ኢህአዴግ/ እንደማይመለከት አስተወቁ”” በዚህ
ተስፋ ያልቆረጠ ህወሓት ሐምሌ 1981 ሁለተኛው ይፋዊ ደብዳቤ ለደርግ መንግስት ላከ፡፡ በፍጥነት የሁለትዮሽ ሰላም ውይይት እንዲጀመርም
በደብዳቤው አፅንኦት ሰጠው፡፡
ኢህአዴግ ግን የላከው ደብዳቤ ምላሽ ለማግኘት ለንደን ለነበሩት የመንግስት ተወካዮች በማግኘት የሰላም ውይይት እንዲፋጠን
መንግስታቸውን እንዲጠይቁ አነጋገራቸው፡፡ በደርግ በኩል የተሰጠ ምላሽ ግን እጅግ አስገራሚ ነበር፡፡ ህወሓትና ኢህዴን መሳሪያቸው
በማስቀመጥ እጃቸው እንዲገቡና ምንም አይነት የበቀል እርምጃ እንደማይወሰድባቸው ሲል ነበር ምላሽ የሰጠ፡፡ እናም በህወሓት በኋላም
በኢህአዴግ የቀረበው የሰላም ጥሪ ለሰባት ወራት ቢጠበቅም ሳይሳካ ቀረ፡፡
እናም ኢህአዴግ ከዘመቻ ሰላም በትግል፣ ዘመቻ ፋና ኢህአዴግ፣ ዘመቻ ቴዎድሮስ፣ ዘመቻ ዋለልኝ፣ ዘመቻ ቢሉሱማ ውልቂጡማ
በሙሉ በኢህአዴግ አጥቂነትና በደርግ ተከላካይነት የተካሄዱ የሁለት አመት ጦርነት አካሄደ፡፡ መዝጊያቸው ደግሞ አዲስ አበባን ጨምሮ
መላው ሃገሪቱ ከደርግ መንግስት ነፃ መውጣታቸው የተበሰረበት ዘመቻ ወጋገን ነው””
የፌዴራል ስርአቱ መምጫው ዋዜማ እና የቶሮንቶው ጉባኤ
የደርግ መንግስት በመጨረሻ ሰዓት የወሰዳቸው የፖለቲካ እርምጃዎች ውድቀቱን ከማፋጠን በቀር የሚታደጉ አልነበሩም፡፡ ሁሉም
ነገር አብቅቶለት ነበር፡፡ ለኤርትራና ትግራይ ልዩ የራስ ገዝ አስተዳደር በመስጠት ፖለቲካዊ መፍትሄ ሰጥቻለሁ ቢልም እጅግ አደርባይ
አዋጅ ነበር፡፡
በ1982 በሐምሌ ወር መጀመሪያ ሳምንት በካናዳ ቶሮንቶ በኢህአፓ ቤተዘመድ ዳኝነት በኢዲዩ፣መኢሶንና ኢህዴአንና መሰሎቻቸው
ታላቅ ኮንፈረንስ ተካሂዶ ነበር፡፡ ኢህአዴግ ኮንፈረንሱን ‹‹የቀኞችና ትምክህተኞች የጨበራ ተዝካር›› በሚል ርእስ ክፉኛ ተችቶታል”” በኮንፈረንሱ በርከት ያሉ የምዕራቡ ዓለም መንግስታት ተወካዮች የተገኙ ሲሆን የጣሊያን መንግስት
በገንዘብ መደገፉ ይታወቃል”” ኮንፈረንሱ በኢህአፓ የተዘጋጀ ጊዜውም ቦታውም በኢህአፓ ተመርጦ የተሳታፊው
ቁጥርና የተሳታፊውም ማንነት በኢህአፓ ተወስኖ በመኢሶን ኢዲዩና ኢፒዲኤ ተባባሪነት በቶሮንቶ በኢትየጵያ መካሄድ ስለሚገባ የሰላማዊ
ሽግግር መድረክ የሚወያይ ኮንፈረንስ ነበር፡፡ በጣም የሚገርመው በኮንፈረንሱ አንድን የብሄር ብሄረሰብ ፖለቲካ ድርጅቶች ቡድኖች
ወይም ወደዚህ ዘመም የሆኑ ሰዎች እንዳይጋበዙ ነበር የተከለከለው፡፡ በወቅቱ ግን ከ10 በላይ ደርግን የሚታገሉ የብሄር ድርጅቶች
ነበሩ፡፡
ኢህአዴግ በቶሮንቶው ኮንፈረንስ ተሰታፊ ለነበሩት ድርጅቶች ባቀረበው ጥሪ መሰረት ከኢፒዴኤ በስተቀር ሌሎቹ ማለትም ኢህአፓ፣
ኢዲዩና መኢሶን የተገኙበት ስብሰባ ለማካሄድ ችሎ ነበር፡፡ በዚህ ህዳር 1983 ዋሽንግተን ላይ በተካሄደው ስብሰባ መኢሶን በአቶ
አበራ የማነአብ፣ ኢዲዩ በልዑል ራስ መንገሻ፣ ኢህአፓ አቶ አሰፋ /ፍስሃ/ ፣ኢህአዴግ በአቶ ብርሃነ ገ/ ክርስቶስ፣ መኮንን ታከለ፣
ዳዊት ዮሃንስና አሰፋ ማሞ ነበር የተወከሉ፡፡
ኢህአዴግ አግላይና ለብሄር ብሄረሰብ ድርጅቶች እውቅና የነፈገ የቶሮንቶ ስህተት እንዲታረምና ሁሉም ሃይሎች የሚሳተፉበት
የሰላም ኮንፈረንስ እንዲዘጋጅ ሃሳበ አቀረበ፡፡ ነገር ግን ኢህአፓና መኢሶን በቶሮንቶ በተጀመረበት መንገድ መቀጠል አለብን ሌላ
መድረክ መፈጠር የለበትም የሚል አቋም በማራመድ ለብዝሃነት እውቅና እንደማይሰጡ በተግባር አሳዩ፡፡
የኢህአዴግ የሰላምና የሽግግር ፕሮግራም
የኢህአዴግ የሰላም ጥረት ባይሳካም እስከመጨረሻ ሰአት የቆመ አልነበረም”” በዚህ መሰረትም ግንቦት 1982 የሰላምና የአንድነት የሽግግር ፕሮግራም ይፋ አደረገ”” በፕሮግራሙም እንዲህ ሲል ፍላጎቱንና አላማውን ግልፅ አድርጎ ነበር፡፡
“የኢህአዴግ ሰላማዊና የዴሞክራሲያዊ የሽግግር ፕሮግራም በኢትዮጵያ ሰላምን ዴሞክራሲና ነፃነት ለማምጣት የሚያስችል ፕሮግራም
በመሆኑ የአገሪቱን ችግሮች ለመፍታት በጣም ተፈላጊ ፕሮግራም ነው” ይላል ፕሮግራሙን ተከትሎ በይፋ ባወጣው መግለጫም ፕሮግራሙን
ለመተግበር ለሁሉም የፖለቲካ ሃይሎች /ደርግን ጭምር/ ጥሪ አድርጓል፡፡ ሁሉም ሃይሎች ደርግም ጭምር በአንድ ሽግግር መንግስት ሆነው
እንዲወዳደሩ እና የኢትዮጵያ ህዝቦች ይበጀኛል የሚሉትን እንዲመርጡ ነፃ ፖለቲካዊ ምህዳር እውን እንዲሆን በመጥቀስ ለመድብለ ፓርቲ
ያለውን አቋም አንፀባረቀ፡፡ ነገር ግን ለኢህአዴግ ጥሪ በአሜሪካና አውሮጳ የነበሩ ፓርቲዎች ኮንፈረንስ በማካሄድ ኢህአዴግ አዲሰ
አበባ እንዳይገባ ሲንጫጩ መዋል መረጡ፡፡ ደርግም “አልሞትባይ ተጋዳይ” ለጥሪው የዝሆን ጀሮ ሰጥቶ በአውዳሚ ጦርነት መሰናበት መረጠ”” ነገር ግን የኢትዮጵያ ህዝብ የኢህአዴግ እንቅስቃሴው ትክክለኛ ፍላጎትና አላማ እንዲረዳ ትልቅ
ፋይዳ ነበረው፡፡
የሽግግር መንግስት፣ የፖለቲካ ድርጅቶች ጥምር መንግስት
በኢትዮጵያ ታሪክ በሀገር ውስጥ የተለያየ የፖለቲካ አላማ አለን የሚሉ ሃይሎች በአንድ አዳራሽ ተገናኘተው የተመካከሩበት
ታሪክ የመጀመሪያ ተደርጎ የሚጠቀሰው የሰኔው 1983 የሰላምና ሽግግር ኮንፈረንስ ነው፡፡ ለዚህ ሲባልም ከሰኔ 24/1983 በፊት
የተመሰረቱ 27 የፖለቲካ ቡድኖች የተሳተፉበት ኮንፈረንስ ተካሄደ፡፡ ኮንፈረንሱ መሰረታዊ የሀገሪቱ ፖለቲካዊ አቅጣጮዎች ምን መሆን
እንዳለበት ፍኖተ ካርታ አውጥቶ በመግባባት ተደመደመ”” ውሳኔውም
በቻርተር የሚመራ የሽግግር መንግስት መመስረት ነበር፡፡
በመሆኑም ያኔ የተመሰረተው የሽግግር መንግስት የድርጅቶች ጥምር መንግስት ነበር፡፡ የሽግግር ቻርተርም ፀደቀ፡፡ የሽግግር
መንግስቱ የተመሰረተውም የኢትዮጰያ ህዝቦች ከሚቀርብላቸው ፖለቲካዊ አማራጮች ውስጥ ይሻለናል ያሉትን እስኪመርጡ ድረስ ሰላማዊና
ዴሞክራሲያዊ ሁኔታን ፈጥሮ መንገዱን የማመቻቸት ነበር”” በኮንፈረንሱም
22 የሚሆኑ አለም አቀፍ አካላትና የመንግስታት ተወካዮች ተገኝተው ነበር፡፡
የኢትዮጵያ ሰላምና ዴሞክራሲያዊ የሽግግር ጉባኤ ቻርተር በነጋሪት ጋዜጣ ሐምሌ 15/1983 የታተመ ሲሆን በመግቢያው
ላይ እንዲህ የሚል ሰፍሮ እናገኘዋለን፡፡
“በኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ከሚገኙት የተለያየ አመለካከት ካላቸው የሰላምና የዴሞክራሲ ሃይሎች ውስጥ የተወከሉ ከሰኔ
24 እስከ ሰኔ 28/1983 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ባደረጉት አገር አቀፍ ጉባኤ ይህንን ለመሸጋሪያ መንግስት መሰረታዊ መመሪያና
ለሽግግር ዘመን መርሆ የሆነው ቻርተር መክረውና ተቀበለው ያፀደቁት በመሆኑ፤ እነሆ እንደሚከተለው ታውጇል፡፡›› ይላል፡፡
የወጣው
ቻርተር ስርአቱን ብቻ ሳይሆን ለስርአቱ ትክክለኛ የመንግስት አወቃቀር ወይም ቅርፅም ፌዴራላዊ መሆን እንዳለበት ያስቀመጠ ነበር፡፡
ይህ በኋላም በፌዴራል ህገ-መንግስቱ አንቀፅ 1 ላይ ከፊት አምጥቶ አስረግጦ አስቀምጦታል “ይህ ህገ መንግስት ፌደራላዊና ዴሞክራሲያዊ የመንግስት አወቃቀርን
ይደነግጋል፡፡” ይላል፡፡