Tuesday, 4 July 2017

የመፍትሔው አባት





አቶ መንግስቱ አስፋው ይባላሉ፡፡ በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ ዘጠኝ ነዋሪ ሲሆኑ የበርካታ አዳዲስ ፈጠራዎች ባለቤት ናቸው፡፡ ባለሙያው ውልደታቸውም ሆነ እድገታቸው እዚሁ አዲስ አበባ ሲሆን ገና ከልጅነታቸው አንስቶ ለፈጠራ ስራ ልዩ ፍላጎትና ተነሳሽነት ነበራቸው”” ችግር ፈቺ የፈጠራ ስራዎችን በወዳደቁ ቁሳቁስ አስመስሎ በመስራት የተለያዩ ሙከራዎችን ሲያደርጉ መቆየታቸውን ያስታውሳሉ፡፡ በዚህም በአካባቢው ህብረተሰብ ዘንድ አድናቆትን አትርፈው እንደነበር የሚገልፁት አቶ መንግስቱ ከ11ኛ ክፍል በኋላ ግን በወቅቱ የኢህአፓ አባል ሆነው በመቀላቀላቸው እንኳንስ የፈጠራ ስራ ሊሰሩ ይቅርና ወጥተው ለመግባትም ትልቅ ፈተና ሆኖባቸው ነበር፡፡

የመፍትሔው አባት






 አቶ መንግስቱ አስፋው ይባላሉ፡፡ በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ ዘጠኝ ነዋሪ ሲሆኑ የበርካታ አዳዲስ ፈጠራዎች ባለቤት ናቸው፡፡ ባለሙያው ውልደታቸውም ሆነ እድገታቸው እዚሁ አዲስ አበባ ሲሆን ገና ከልጅነታቸው አንስቶ ለፈጠራ ስራ ልዩ ፍላጎትና ተነሳሽነት ነበራቸው”” ችግር ፈቺ የፈጠራ ስራዎችን በወዳደቁ ቁሳቁስ አስመስሎ በመስራት የተለያዩ ሙከራዎችን ሲያደርጉ መቆየታቸውን ያስታውሳሉ፡፡ በዚህም በአካባቢው ህብረተሰብ ዘንድ አድናቆትን አትርፈው እንደነበር የሚገልፁት አቶ መንግስቱ ከ11ኛ ክፍል በኋላ ግን በወቅቱ የኢህአፓ አባል ሆነው በመቀላቀላቸው እንኳንስ የፈጠራ ስራ ሊሰሩ ይቅርና ወጥተው ለመግባትም ትልቅ ፈተና ሆኖባቸው ነበር፡፡

የደርግ ካድሬዎችም በተደጋጋሚ ጊዜ ማስጠንቀቂያና ከዛም ባለፈ ሊገድሏቸው ሲሉ ህይወታቸውን ለማትረፍ ቤተሰብ እንኳ ሳይሰናበቱ ትምህርታቸውን አቋርጠው ሽሽትን መረጡ፡፡ ከትውልድ ቀያቸውም ርቀው ከቀን ሰራተኛነት ጀምሮ በአናፂና ግንበኛነት እንዲሁም እስከ መንግስት ሰራተኛነት ያገኙትን ስራ በስጋትና በሰቆቃ በመስራት በነቀምት፣ በባህርዳር፣ በደጀንና ከዛም ወደ አሰብ በማቅናት አስቸጋሪ ህይወት አሳልፈዋል፡፡