Wednesday, 24 May 2017

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ-መንግስት መሰረታዊ ዓላማዎች

የኢ... ሕገ-መንግስት የኢትዮጵያ ህዝቦች በሃገራቸው መፃኢ ዕድል ላይ ብሩህ ተስፋ ሰንቀው እንደ አንድ ማህበረሰብ እንዲነሳሱ የሚያደርጋቸውን ዓላማ ያስቀመጠ ነው፡፡ ዓላማዎቹ በህገ-መንግስቱ መግቢያ ላይ የሰፈሩ ናቸው፡ ይህም አጠር ባለ መንገድ ሲገለፅ ያለፈውን የተዛባ ግንኙነት በማስተካከል እና ባለፈው ያፈሩትን የጋራ ሃብት፣ ትስስርና እሴት ስላላቸው በፍላጎታቸውና በራሳቸው ፈቃድ ዘላቂ ሰላም፣ ዋስትና ያለው ዴሞክራሲ እንዲሰፍን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገታቸው እንዲፋጠን የሚያስችል የጋራ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ማህበረሰብ ለመገንባት ቃል የገቡ መሆናቸውን፣ ይህን ለማሳካት የግለሰብም ሆነ የብሄሮች ብሄረሰቦች ህዝቦች መብቶችና የፆታ እኩልነት ማረጋገጥ፣ ባህሎችና ሃይማኖቶች ያለ አድሎና ልዩነት እንዲራመዱ ማድረግ ፅኑ እምነታቸው እንደሆነ መወሰናቸውን …. የሚል ነው፡፡ የሕገ-መንግስታችን መግቢያ ዘላቂ ሰላም፣ ዋስትና ያለው ዴሞክራሲ፣ ፈጣን ኢኮኖሚያዊ ልማት፣ አንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ግንባታ የሚሉ ዓላማዎችና ራዕዮች በግልፅ አስቀምጧል፡፡ እነዚህ የህገ-መንግስታችን ዓላማዎች የማይነጣጠሉና እርስ በርሳቸው የተሳሰሩ ናቸው፡፡