Saturday, 29 August 2015

GTP I የተፈፀመበት አግባብና ውጤቱ ከህዳሴያችን አንፃር የነበረው ፋይዳ!! ከብሩክ ከድር(part 2)



GTP I የተፈፀመበት አግባብና ውጤቱ ከህዳሴያችን አንፃር የነበረው ፋይዳ 
የመጀመሪያው ዙር ዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ፈጣን፣ ተከታታይና ፍትሃዊነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት ማስመዝገብና መዋቅራዊ ለውጥ ማምጣት ላይ ትኩረት አድርጎ ሲፈፀም የቆየ ሲሆን በርካታ አንፀባራቂ ውጤቶችም የተመዘገቡበትና ለሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሸን ዘመን እቅድ ጠቃሚ ልምዶች የተገኙበት ነበር፡፡ የሀገራችንን ህዳሴ ማረጋገጥ የምንችለው የተለጠጡና ወገብ የሚያጎብጡ እቅዶችን አቅደን በመተግበር ብቻ መሆኑን ታምኖበት ተግባራዊ በመደረጉ የጀመርነውን የዕድገት ግስጋሴ ከፍ ወዳለ ደረጃ ለማድረስ አስችሏል፡፡ በየደረጃው ከአመራር እስከ ህዝብ ድረስ በተደረጉ ጥልቀት ያላቸው ግምገማዎች እቅዱ በአግባቡ ተገምግሞ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል፡፡ የአፈፃፀም ግምገማው እንደሚያመለክተው ከተቀመጡ ግቦች ውስጥ ቀድመው የተሳኩ፣ በእቅዱ መሰረት የተሳኩ ግቦችና በተለያዩ ምክንያቶች በግባችን መሰረት ያልተሳኩ ግቦች መኖራቸውን መገምገም ተችሏል፡፡ በመላ ህዝባችን ከፍተኛ ንቅናቄ ታጅበን የፈፀምነው የመጀመሪያው 5 ዓመት እቅድ በብዙ መልኩ ስኬታማና ጠቃሚ ሀገራዊ ልምዶችም የተወሰዱበት እንደነበር መውሰድ ይቻላል፡፡  
የኢኮኖሚ ዕድገትና የህዝብ ተጠቃሚነትን ከማረጋገጥ አንፃር በአማካይ 10.1 በመቶ ዕድገት ማስመዝገብ የተቻለ ሲሆን በከተማችን በአማካይ በ15 በመቶ በላይ ፈጣን እድገት ተመዝግቧል፡፡  የኢኮኖሚ ዕድገቱ ከፍተኛ የስራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን ዓመታዊ አማካይ የነፍስ ወከፍ ገቢያችን በሀገር አቀፍ ደረጃ 700 ዶላር ደርሷል፡፡ በከተማችን የድህነት ምጣኔው በ1997 ከነበረበት 38.7 በመቶ በ2007 ወደ 22 በመቶ ዝቅ እንደሚል ተገምቷል፡፡ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ለውጥን ስንመለከት ከ2003-2006 ባሉት አራት ዓመታት የአገልግሎት ዘርፍ በ2003 64.18 % የነበረው በ2006 ወደ 62.6% ዝቅ ያለ ሲሆን የኢንዱስትሪ ዘርፍ ደግሞ ከ34.79 % ወደ 34.46% ከፍ ብሏል፡፡ ከዚህ በመነሳት መረዳት የሚቻለው የከተማው አብዛኛው ኢኮኖሚ የሚመነጨው ከአገልግሎት ዘርፍ መሆኑን ነው፡፡ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ለውጥ ማረጋገጥ ለእድገታችን ዘላቂነትና ወደ መካከለኛ ገቢ ኢኮኖሚ ለምናደርገው ጉዞ ወሳኝ በመሆኑ በመጀመሪያው ዙር የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ከተጠበቀው ይልቅ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር በከተማችን ወደ አገልግሎት ዘርፍ ያዘነበለ ነበር፡፡ የአገልግሎት ዘርፍ ማደግ በከተማችን ኢኮኖሚ ውስጥ ያለው ፋይዳ እንደተጠበቀ ሆኖ የኢኮኖሚውን ምርታማነት፣ የስራ ዕድልና የገበያ አቅም ለመፍጠር በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ልማት ላይ እመርታ ማምጣት የሞት የሽረት ጉዳይ ተደርጎ ሊወሰድ የሚገባው ነው፡፡  
የመሰረተ ልማት ፕሮግራሞችን በማሳካት ረገድ በኤሌክትሪክ ሀይል አቅርቦት፣ የመንገድ መሰረተ ልማት ዝርጋታ፣ የባቡር መንገድ ዝርጋታ፣ የቴሌኮሚኒኬሽን አገልግሎት በማዳራስ፣ ንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትን በማሳደግ ረገድ አመርቂ ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡ በማህበራዊ ልማት ረገድ የትምህርት ስርጭትና ሽፋን በማሳደግ እንዲሁም የጤና አገልግሎትን በማዳረስ ረገድ አንፀባራቂ ውጤቶች ተመዝገበዋል፡፡ የማስፈጸም አቅም ግንባታና ልማታዊ መልካም አስተዳደርን በማረጋገጥም ረገድ እንዲሁ ያለው የእቅድ ምዕራፍ ትርጉም ያለው ርቀት መሄድ ተችሏል፡፡ በአጠቃላይ አፈፃፀማችን የሚያመለክተው መካከለኛ ገቢ ያለው ዜጋና ከተማ ለመፍጠር የያዝነው ራዕይ ከተቀመጠው ጊዜ አስቀድመን ማሳካት እንደሚቻል ሲሆን አሁንም ትርጉም ባለው ደረጃ በከተማዋ ውስጥ የሚታየውን ድህነት ለመቅረፍ ቀን ከሌት መስራት የሚጠበቅብን መሆኑንንም መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ 
እነዚህንና ሌሎች ሀገራዊና ከተማ አቀፍ ስኬቶች እንደተጠበቁ ሆነው በሁሉም መስክ ያስመዘገብናቸው ለውጦች በመጠን ረገድ ጎልተው የወጡ ቢሆንም በሚፈለገው መጠን ጥራትን በማረጋገጥ ረገድ ክፍተቶች አሉ፡፡ ብቁ፣ ጥራት ያለውና ተወዳዳሪ ሆኖ ለመገኘት በየመስኩ ርብርብ ማድረግ ይጠይቀናል፡፡ የህዝብ ፍላጎት አዳጊ መሆንና ሞጋች ህብረተሰብ እየተፈጠረ ከመሄዱ አኳያ ይህንን ሁኔታ በተጨባጭ የተረዳ እንቅስቃሴ ሊኖረን ይገባል፡፡
የመጀመሪያው ዙር እቅድ ስኬታማ ሊሆን የቻለው የእቅዱ ፈፃሚ ሀይሎች በተደራጀ ንቅናቄ በመንቀሳቀሳቸው በተለይም ህዝቡ በእቅዶቹ ዙሪያ እየመከረ፣ አፈፃፀማቸውን እየገመገመ፣ ሲፈጸሙ በባለቤትነት የእቅዱ ፈፃሚ ሆኖ መረባረብ በመቻሉ ነው፡፡ ይህም በሁለተኛው ምዕራፍ እቅድ ይበልጥ እየተረጋጋጠ ሊሄድ የሚገባው ነው፡፡ የእቅዱ ዋነኛ ባህሪ መሰረታዊ የአመለካከት ለውጥና ሽግግርን (transformation) ማምጣት ላይ ትኩረት ያደረገ ከመሆኑ አኳያ የልማት ሀይሎች የነቃ ተሳትፎ ተኪ የሌለው ሚና ይጫወታል፡፡ ሁለተኛው ዕቅድ ረቂቅ ለህዝብ ውይይት በቀረበበት ወቅት በከተማችን በተከፈቱ የህዝብ መድረኮች መረዳት እንደተተቻለው ለቀጣዩ እቅድ ስኬታማነት ህዝቡ ከምንጊዜውም በላቀ ሁኔታ ድጋፉን የሰጠ መሆኑን ነው፡፡ በ10ኛው የድርጅታችን ኢህአዴግ ድርጅታዊ ጉባዔ ላይም ረቂቅ እቅድ ፀድቆ ከቀጣዩ በጀት ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ መደረግ የሚጀምር ሲሆን ለዚህ እቅድ ተፈፃሚነት በየደረጃው ያለ አመራራችንና መዋቅራችን በከፍተኛ ወኔና እልህ መንቀሳቀስ ይጠበቅባቸዋል፡፡   
GTP II ከህዳሴያችን አንፃር ምን ትርጉም ይኖረዋል?
የልማታዊ ዴሞክራሲያዊ መስመራችን በተሞክሮነት የሚወስዳቸው የምስራቅ ኢስያ ፈጣን ኢኮኖሚ ያስመዘገቡ ሀገራት (Asian Tigers) ወይም The Four Asian Dragons የምንላቸው ታይዋን፣ ደቡን ኮሪያ፣ ሆንግ ኮንግና ሲንጋፖር ከ1960ዎቹ እስከ 1990ዎቹ መጨረሻ ድረስ ፈጣንና ተከታታይነት ያለው አስደናቂ እድገት በልማታዊ መንገድ ማስመዘገብ ችለዋል፡፡ ህዝባቸውን ከድህነት በማውጣት ዛሬ ሀገራቱ በዓለም ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ መፍጠር የሚችሉ ሀገራት ሆነዋል፡፡ ደቡብ ኮሪያና ታይዋን በአይቲ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ በዓለም ቀዳሚ ሀገራት ናቸው፡፡ ሆንግ ኮንግና ሲንጋፖር ደግሞ በዓለም በመሪነት የሚቀመጡ የፋይናንስ ማዕከላት መሆን ችለዋል፡፡ እነዚህ ሀገራት እዚህ ደረጃ ላይ መድረስ የቻሉት በተከታታይ ሊያሰሩ የሚችሉ እቅዶችን አቅደው፣ ወገባቸውን ጠበቅ አድርገው መፈጸም በመቻላቸውና ልማታዊ አመራር ጥበብን በመከተላቸው ነው፡፡     
ከዓለም ፈጣን ኢኮኖሚዎች ውስጥ አንዱ የቻይና ኢኮኖሚ ነው፡፡ በዓመታዊ ጠቅላላ ምርት ሁለተኛው የዓለም ትልቁ ኢኮኖምም ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ ባለፉት 30 ዓመታት ኢኮኖሚያቸው በአማካይ በ10 መቶ ሲያድግ ቆይቷል፡፡ ይህም ሆኖ ግን እንደ ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) ሪፖርት መሰረት ከድህነት ወለል በታች 6.1 በመቶ ህዝብ ይኖርባታል፡፡ ቻይና ከ1953 ጀምሮ እስከ 2015 ድረስ 12 ጊዜ ያህል ተከታታይ የ5 ዓመታት እቅድ ስትተገብር ቆይታለች፡፡ በዚህ ውስጥ ከ1958-1962 ድረስ የነበረው ሁለተኛው ዙር እቅድ ታላቁ እመርታዊ ለውጥ የሚል ስያሜ ነበረው፡፡ ሌሎች በመሃል ያሉ የስትራቴጂክ እቅድ ዓመታት የየራሳቸው ስያሜና ልዩ የትኩረት ማዕከላት ነበሯቸው፡፡ በእነዚህ ዓመታት ውስጥ በተከታታይ ሲተገበር በነበረው እቅድ ውስጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ ሀገሪቱን ወደ ኢንዱስትሪ ማዕከልነት በመቀየር፣ በድህነት ውስጥ ያለን ህዝብ የማውጣትና ሀገሪቱን የማዘመን ስራዎች ትኩረት ተሰጥቷቸው ስለተመሩ ዛሬ ቻይናን ባለ ግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤትነት አምጥተዋል፡፡     
እኛ የመጀመሪያውን ዙር የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ በስኬት አጠናቀን ወደ ሁለተኛው ስንሄድ የወጣነው ደገት ቢኖርም አሁንም አሁንም እጅግ ብዙ ያልወጣነው ደገት መኖሩን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ ህዳሴያችን የተከታታይ ትውልዶች ትግልን የሚጠይቅና ጉዞው ያለምንም መሰነካከል ፍጥነቱን ጠብቆ እንዲቀጥል ማድረግ ይገባል፡፡ ከድቅድቅ ጨለማ ወጥተን የብርሃን ዘመንን ለማምጣት የምስራቅ ኢሲያ ሀገራት ያለፉበትን ውጣ ውረድ፣ የረገጡት ድንጋይ መርገጥና የከፈሉትን መሰዋዕትነት ይበልጥ መክፈል ይጠይቃል፡፡ ዛሬ የጀመርነው የህዳሴ ጉዞ የነገዋን ኢትዮጵያ በማበጀት ሂደት ውስጥ ያለውን ከፍተኛ ትርጉም በመረዳት በላቀ እልህና ወኔ ለቀጣዩ ተልዕኮ በየመስኩ ራስን ማዘጋጀት ያስፈልጋል፡፡
  
 

የኢትዮጵያ ህዳሴና GTP II ( GTP I የተፈፀመበት አግባብና ውጤቱ ከህዳሴያችን አንፃር የነበረው ፋይዳ ከብሩክ ከድር (part 2)



GTP I የተፈፀመበት አግባብና ውጤቱ ከህዳሴያችን አንፃር የነበረው ፋይዳ 
የመጀመሪያው ዙር ዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ፈጣን፣ ተከታታይና ፍትሃዊነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት ማስመዝገብና መዋቅራዊ ለውጥ ማምጣት ላይ ትኩረት አድርጎ ሲፈፀም የቆየ ሲሆን በርካታ አንፀባራቂ ውጤቶችም የተመዘገቡበትና ለሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሸን ዘመን እቅድ ጠቃሚ ልምዶች የተገኙበት ነበር፡፡ የሀገራችንን ህዳሴ ማረጋገጥ የምንችለው የተለጠጡና ወገብ የሚያጎብጡ እቅዶችን አቅደን በመተግበር ብቻ መሆኑን ታምኖበት ተግባራዊ በመደረጉ የጀመርነውን የዕድገት ግስጋሴ ከፍ ወዳለ ደረጃ ለማድረስ አስችሏል፡፡ በየደረጃው ከአመራር እስከ ህዝብ ድረስ በተደረጉ ጥልቀት ያላቸው ግምገማዎች እቅዱ በአግባቡ ተገምግሞ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል፡፡ የአፈፃፀም ግምገማው እንደሚያመለክተው ከተቀመጡ ግቦች ውስጥ ቀድመው የተሳኩ፣ በእቅዱ መሰረት የተሳኩ ግቦችና በተለያዩ ምክንያቶች በግባችን መሰረት ያልተሳኩ ግቦች መኖራቸውን መገምገም ተችሏል፡፡ በመላ ህዝባችን ከፍተኛ ንቅናቄ ታጅበን የፈፀምነው የመጀመሪያው 5 ዓመት እቅድ በብዙ መልኩ ስኬታማና ጠቃሚ ሀገራዊ ልምዶችም የተወሰዱበት እንደነበር መውሰድ ይቻላል፡፡  
የኢኮኖሚ ዕድገትና የህዝብ ተጠቃሚነትን ከማረጋገጥ አንፃር በአማካይ 10.1 በመቶ ዕድገት ማስመዝገብ የተቻለ ሲሆን በከተማችን በአማካይ በ15 በመቶ በላይ ፈጣን እድገት ተመዝግቧል፡፡  የኢኮኖሚ ዕድገቱ ከፍተኛ የስራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን ዓመታዊ አማካይ የነፍስ ወከፍ ገቢያችን በሀገር አቀፍ ደረጃ 700 ዶላር ደርሷል፡፡ በከተማችን የድህነት ምጣኔው በ1997 ከነበረበት 38.7 በመቶ በ2007 ወደ 22 በመቶ ዝቅ እንደሚል ተገምቷል፡፡ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ለውጥን ስንመለከት ከ2003-2006 ባሉት አራት ዓመታት የአገልግሎት ዘርፍ በ2003 64.18 % የነበረው በ2006 ወደ 62.6% ዝቅ ያለ ሲሆን የኢንዱስትሪ ዘርፍ ደግሞ ከ34.79 % ወደ 34.46% ከፍ ብሏል፡፡ ከዚህ በመነሳት መረዳት የሚቻለው የከተማው አብዛኛው ኢኮኖሚ የሚመነጨው ከአገልግሎት ዘርፍ መሆኑን ነው፡፡ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ለውጥ ማረጋገጥ ለእድገታችን ዘላቂነትና ወደ መካከለኛ ገቢ ኢኮኖሚ ለምናደርገው ጉዞ ወሳኝ በመሆኑ በመጀመሪያው ዙር የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ከተጠበቀው ይልቅ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር በከተማችን ወደ አገልግሎት ዘርፍ ያዘነበለ ነበር፡፡ የአገልግሎት ዘርፍ ማደግ በከተማችን ኢኮኖሚ ውስጥ ያለው ፋይዳ እንደተጠበቀ ሆኖ የኢኮኖሚውን ምርታማነት፣ የስራ ዕድልና የገበያ አቅም ለመፍጠር በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ልማት ላይ እመርታ ማምጣት የሞት የሽረት ጉዳይ ተደርጎ ሊወሰድ የሚገባው ነው፡፡  
የመሰረተ ልማት ፕሮግራሞችን በማሳካት ረገድ በኤሌክትሪክ ሀይል አቅርቦት፣ የመንገድ መሰረተ ልማት ዝርጋታ፣ የባቡር መንገድ ዝርጋታ፣ የቴሌኮሚኒኬሽን አገልግሎት በማዳራስ፣ ንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትን በማሳደግ ረገድ አመርቂ ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡ በማህበራዊ ልማት ረገድ የትምህርት ስርጭትና ሽፋን በማሳደግ እንዲሁም የጤና አገልግሎትን በማዳረስ ረገድ አንፀባራቂ ውጤቶች ተመዝገበዋል፡፡ የማስፈጸም አቅም ግንባታና ልማታዊ መልካም አስተዳደርን በማረጋገጥም ረገድ እንዲሁ ያለው የእቅድ ምዕራፍ ትርጉም ያለው ርቀት መሄድ ተችሏል፡፡ በአጠቃላይ አፈፃፀማችን የሚያመለክተው መካከለኛ ገቢ ያለው ዜጋና ከተማ ለመፍጠር የያዝነው ራዕይ ከተቀመጠው ጊዜ አስቀድመን ማሳካት እንደሚቻል ሲሆን አሁንም ትርጉም ባለው ደረጃ በከተማዋ ውስጥ የሚታየውን ድህነት ለመቅረፍ ቀን ከሌት መስራት የሚጠበቅብን መሆኑንንም መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ 
እነዚህንና ሌሎች ሀገራዊና ከተማ አቀፍ ስኬቶች እንደተጠበቁ ሆነው በሁሉም መስክ ያስመዘገብናቸው ለውጦች በመጠን ረገድ ጎልተው የወጡ ቢሆንም በሚፈለገው መጠን ጥራትን በማረጋገጥ ረገድ ክፍተቶች አሉ፡፡ ብቁ፣ ጥራት ያለውና ተወዳዳሪ ሆኖ ለመገኘት በየመስኩ ርብርብ ማድረግ ይጠይቀናል፡፡ የህዝብ ፍላጎት አዳጊ መሆንና ሞጋች ህብረተሰብ እየተፈጠረ ከመሄዱ አኳያ ይህንን ሁኔታ በተጨባጭ የተረዳ እንቅስቃሴ ሊኖረን ይገባል፡፡
የመጀመሪያው ዙር እቅድ ስኬታማ ሊሆን የቻለው የእቅዱ ፈፃሚ ሀይሎች በተደራጀ ንቅናቄ በመንቀሳቀሳቸው በተለይም ህዝቡ በእቅዶቹ ዙሪያ እየመከረ፣ አፈፃፀማቸውን እየገመገመ፣ ሲፈጸሙ በባለቤትነት የእቅዱ ፈፃሚ ሆኖ መረባረብ በመቻሉ ነው፡፡ ይህም በሁለተኛው ምዕራፍ እቅድ ይበልጥ እየተረጋጋጠ ሊሄድ የሚገባው ነው፡፡ የእቅዱ ዋነኛ ባህሪ መሰረታዊ የአመለካከት ለውጥና ሽግግርን (transformation) ማምጣት ላይ ትኩረት ያደረገ ከመሆኑ አኳያ የልማት ሀይሎች የነቃ ተሳትፎ ተኪ የሌለው ሚና ይጫወታል፡፡ ሁለተኛው ዕቅድ ረቂቅ ለህዝብ ውይይት በቀረበበት ወቅት በከተማችን በተከፈቱ የህዝብ መድረኮች መረዳት እንደተተቻለው ለቀጣዩ እቅድ ስኬታማነት ህዝቡ ከምንጊዜውም በላቀ ሁኔታ ድጋፉን የሰጠ መሆኑን ነው፡፡ በ10ኛው የድርጅታችን ኢህአዴግ ድርጅታዊ ጉባዔ ላይም ረቂቅ እቅድ ፀድቆ ከቀጣዩ በጀት ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ መደረግ የሚጀምር ሲሆን ለዚህ እቅድ ተፈፃሚነት በየደረጃው ያለ አመራራችንና መዋቅራችን በከፍተኛ ወኔና እልህ መንቀሳቀስ ይጠበቅባቸዋል፡፡   
GTP II ከህዳሴያችን አንፃር ምን ትርጉም ይኖረዋል?
የልማታዊ ዴሞክራሲያዊ መስመራችን በተሞክሮነት የሚወስዳቸው የምስራቅ ኢስያ ፈጣን ኢኮኖሚ ያስመዘገቡ ሀገራት (Asian Tigers) ወይም The Four Asian Dragons የምንላቸው ታይዋን፣ ደቡን ኮሪያ፣ ሆንግ ኮንግና ሲንጋፖር ከ1960ዎቹ እስከ 1990ዎቹ መጨረሻ ድረስ ፈጣንና ተከታታይነት ያለው አስደናቂ እድገት በልማታዊ መንገድ ማስመዘገብ ችለዋል፡፡ ህዝባቸውን ከድህነት በማውጣት ዛሬ ሀገራቱ በዓለም ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ መፍጠር የሚችሉ ሀገራት ሆነዋል፡፡ ደቡብ ኮሪያና ታይዋን በአይቲ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ በዓለም ቀዳሚ ሀገራት ናቸው፡፡ ሆንግ ኮንግና ሲንጋፖር ደግሞ በዓለም በመሪነት የሚቀመጡ የፋይናንስ ማዕከላት መሆን ችለዋል፡፡ እነዚህ ሀገራት እዚህ ደረጃ ላይ መድረስ የቻሉት በተከታታይ ሊያሰሩ የሚችሉ እቅዶችን አቅደው፣ ወገባቸውን ጠበቅ አድርገው መፈጸም በመቻላቸውና ልማታዊ አመራር ጥበብን በመከተላቸው ነው፡፡     
ከዓለም ፈጣን ኢኮኖሚዎች ውስጥ አንዱ የቻይና ኢኮኖሚ ነው፡፡ በዓመታዊ ጠቅላላ ምርት ሁለተኛው የዓለም ትልቁ ኢኮኖምም ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ ባለፉት 30 ዓመታት ኢኮኖሚያቸው በአማካይ በ10 መቶ ሲያድግ ቆይቷል፡፡ ይህም ሆኖ ግን እንደ ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) ሪፖርት መሰረት ከድህነት ወለል በታች 6.1 በመቶ ህዝብ ይኖርባታል፡፡ ቻይና ከ1953 ጀምሮ እስከ 2015 ድረስ 12 ጊዜ ያህል ተከታታይ የ5 ዓመታት እቅድ ስትተገብር ቆይታለች፡፡ በዚህ ውስጥ ከ1958-1962 ድረስ የነበረው ሁለተኛው ዙር እቅድ ታላቁ እመርታዊ ለውጥ የሚል ስያሜ ነበረው፡፡ ሌሎች በመሃል ያሉ የስትራቴጂክ እቅድ ዓመታት የየራሳቸው ስያሜና ልዩ የትኩረት ማዕከላት ነበሯቸው፡፡ በእነዚህ ዓመታት ውስጥ በተከታታይ ሲተገበር በነበረው እቅድ ውስጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ ሀገሪቱን ወደ ኢንዱስትሪ ማዕከልነት በመቀየር፣ በድህነት ውስጥ ያለን ህዝብ የማውጣትና ሀገሪቱን የማዘመን ስራዎች ትኩረት ተሰጥቷቸው ስለተመሩ ዛሬ ቻይናን ባለ ግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤትነት አምጥተዋል፡፡     
እኛ የመጀመሪያውን ዙር የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ በስኬት አጠናቀን ወደ ሁለተኛው ስንሄድ የወጣነው ደገት ቢኖርም አሁንም አሁንም እጅግ ብዙ ያልወጣነው ደገት መኖሩን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ ህዳሴያችን የተከታታይ ትውልዶች ትግልን የሚጠይቅና ጉዞው ያለምንም መሰነካከል ፍጥነቱን ጠብቆ እንዲቀጥል ማድረግ ይገባል፡፡ ከድቅድቅ ጨለማ ወጥተን የብርሃን ዘመንን ለማምጣት የምስራቅ ኢሲያ ሀገራት ያለፉበትን ውጣ ውረድ፣ የረገጡት ድንጋይ መርገጥና የከፈሉትን መሰዋዕትነት ይበልጥ መክፈል ይጠይቃል፡፡ ዛሬ የጀመርነው የህዳሴ ጉዞ የነገዋን ኢትዮጵያ በማበጀት ሂደት ውስጥ ያለውን ከፍተኛ ትርጉም በመረዳት በላቀ እልህና ወኔ ለቀጣዩ ተልዕኮ በየመስኩ ራስን ማዘጋጀት ያስፈልጋል፡፡
  
  

የኢትዮጵያ ህዳሴና GTP II ከብሩክ ከድር (part 1)




የኢትዮጵያ ሚሊኒየም (2000 ዓ.ም) ዋዜማ አዲሱን ሺህ ዓመት ስንቀበል በሚሊኒየም አደራሽ በተደረገ መርሃ ግብር ላይ ታላቁ መሪያችን መለስ ዜናዊ ‹‹መጪው ዘመን የኢትዮጵያ ህዳሴ ይሆናል!!›› ማለታቸው ይታወሳል፡፡ ያሳለፍነው ሚሊኒየም ሀገራችን በአንድ ወቅት ከዓለም ታላላቅ ስልጣኔዎች መካከል የነበረችበትና በሂደትም ፀጋዋን በአግባቡ መጠቀም ባለመቻሏና ብዝኃነቷን በብቃት መምራት የሚያስችል ሁኔታ ባለመፈጠሩ ቀደሞ የነበራት ዝናና ገናናነት በሂደት በማሽቆልቆል የተተካበት ሁኔታም ተፈጥሯል፡፡ በማያቋርጥ የኋሊዮሽ ጉዞ ያለፈችበት ወቅትም ነበር፡፡
ታላቁ መሪያችን መለስ ዜናዊ በሚሊኒየም አደራሽ ባደረጉት ንግግር ‹‹ላለፍንበት ሁኔታ ተጠያቂዎቹ እኛና እኛው ብቻ ነን፡፡›› በሚል ያስቀመጡት ሀሳብ የሚያመለክተን የተሻለች ሀገርን ለቀጣዩ ትውልድ ማስረከብ እስካልቻልን ድረስ የትውልድ ተጠያቂነትም የማይቀር እውነታ መሆኑን ነው፡፡ ሀገራችን ወደ ቀድሞ ገናናነት ዘመኗ ዳግም የመመለስ ጉዞ የህዳሴ (renaissance) እቅዳችን መነሻም ከዚህ እልህና ቁጭት የሚነሳ ነው፡፡     
የኢትዮጵያ ህዳሴ የሚለው ፅንሰ ሀሳብ በተግባርም ሆነ በንድፈ ሀሳብ ደረጃ በሀገር ውስጥም ይሁን በውጪው ማህበረሰብ ዘንድ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተለመደ የመጣ ጉዳይ ሆኗል፡፡ ይህ ጽንሰ ሀሳብ ለኢትዮጵያዊያን ያለው ትርጉም ላቅ ያለና ነገን በዛሬ የመስራት ያህል ነው፡፡ በአንድ ወቅት በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ ለነበረችና ዜጎቿ በድህነትና በከፋ ረሃብ ሲማቅቁ የነበሩባትን ሀገር ወደ ከፍታ ዘመን የሚመልስ ታላቅ ሀገራዊ ፍኖተ ካርታ (roadmap) ነው፡፡ የኢትዮጵያ ህዳሴ ማለት በዓለም አደባባይ ተሰሚነታችን ጎልቶ የሚወጣበትን ታሪክ በጋራ ጥረታችን የምንገነባባት ቁልፍ የርብርብ ማዕከል ነው፡፡ይህም በመሆኑ በዛሬውና በነገው ትውልድ መካከል ለሀገራዊ ቅብብል ድልድይ ሆኖ የሚያገለግል የርብርብ አጀንዳችንም ጭምር ተደርጎ ይወሰዳል፡፡   
የኢትዮጵያ ህዳሴ መሰረት የተጣለው መቼ ነው?
የሀገራችን ህዳሴ መሰረት የተጣለው መቼ ነው ካልን ለሁለት ወቅቶች ከፍተኛ ትርጉም መስጠት ያስፈልጋል፡፡ ቀዳሚው ወቅት አፋኙ የደርግ ስርዓት በህዝባዊ ትግል የተገረሰሰበት ወቅት ነው፡፡ የድህነት ዘበኛ፣ የብዝሃነት ጠላት፣ የትምክህተኝነት ወኪልና የግዛት አንድነት አቀንቃኝ የነበረው ደርግ በከፋና እልህ አስጨራሽ ትግል መወገዱ ለሀገራችን ህዳሴ ቀዳሚው መሰረት ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል፡፡ ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ የህዳሴያችን መሰረት ይበልጥ የተጣለውና በአስተማማኝ መልኩ ነጥሮ የወጣው የዛሬ አስራ አራት ዓመት የተሃዳሶው መስመር ጠርቶ በወጣበት ወቅት ነው፡፡ ምንም እንኳ በህዝባዊ የትጥቅ ትግል ደርግ ከተወገደ በኋላ ሀገራችን ፊቷን ወደ ሰላምና መረጋገት፣ ልማትና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ አዙራ የነበረ ቢሆንም የመድረኩን ባህሪ በትክክል ተረድቶ የጠራ አሰላለፍ ያለው ትግል በማድረግ በኩል ግን የውስጠ ድርጅት አደጋዎች አጋጥመው እንደነበር ይታወሳል፡፡ በወቅቱ ያጋጠመውን ውስጣዊ የመበስበስ አደጋ በከፍተኛ ብስለት ያለምንም ደም መፋሰስ በሀሳብ ትግል አሸናፊነት በመጠናቀቁ በወሳኝ መልኩ የሀገራችን ህዳሴ መሰረት እንዲጣል አድርጓል፡፡  
 የሀገራችን ቁልፍ ጠላት ከድህነት በላይ ሊሆን እንደማይችል፣ ትግላችን በኪራይ ሰብሳቢነትና በልማታዊነት መካከል እንደሆነ፣ ሀገራችንን ከከፋ ድህነትና ኋላ ቀርነት አውጥተን ወደ ብልፅግና ዘመን ለማምራት ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር በተደራጀ የህዝብ ተሳትፎ መንቀሳቀስ እንደሚገባን ያስቀመጥበት ወቅት ነበር፡፡ ባለፉት የተሃዳሶው ዘመናት በወቅቱ የተጠቀመጡት የመታገያ አጀንዳዎች ተለቅመው መተግባር ጀምረዋል፣ ፍሬያቸውም በመታየት ላይ ነው፡፡ ዛሬ ላይ ሆነን ያለፉት የተሃድሶው ዓመታት ስናይ ሀገራችንን ከድህነት አረንቋ ለማውጣት የሞት የሽረት ጉዳይ ማድረግ እስካልቻልን ድረስ ሀገራዊ ህልውናችን ጭምር አደጋ ላይ እንደሚወድቅ የተቀመጠው አቅጣጫ ትክክለኛና ወደፊት የምናደርገውን ግስጋሴ  ያፈጠነ እንደነበር መውሰድ ይቻላል፡፡        

የኢትዮጵያ ህዳሴ ማረጋገጫዎች 
ሀገራችን ህዳሴዋን እያረጋገጠች ስለመሆኑ በርካታ ማሳያዎች ማቅረብ ይቻላል፡፡ ከብዙ ማሳያዎች ውስጥ ግን ከፍተኛ ትርጉም ያላቸውን የተወሰኑ ጉዳዮች በማንሳት የኢትዮጵያ ህዳሴ በየመስኩ እየተረጋገጠ ስለመሆኑ ማሳየት ይቻላል፡፡ ቀዳሚው የህዳሴያችን ማረጋገጫ በወሳኝ ሀገራዊ ጉዳዮች እየተፈጠረ ያለው ብሔራዊ መግባባት ነው፡፡ ከወርቃማው ታሪካችን እንደምንገነዘበው የሀገራችን ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በጋራ ጉዳይ ቆመው በአንድነት ጠላትነት ፋሽስት ጣሊያንን የመከቱበት የአድዋ ድልን ያህል አሁንም በድህነት ላይ በጋራ ለመዝመት የተነሳሳንበት ወቅት ተፈጥሯል፡፡ ብሔራዊ መግባባት በጥቃቅን ጉዳዮች ላይ ጭምር በጋራ መቆምን የግድ የሚል ፍልስፍና ሳይሆን በወሳኝ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ባጋራ መቆምን የሚጠይቅ አስተሳሰብ ነው፡፡ ከዚህ አንፃር ከታየ በህገ መንግስታችን፣ በጋራ ጠላቶቻችን ዙሪያ እየፈጠርነው ያለ መግባባት ህዳሴያችንን እውን ከማድረግ አኳያ የራሳቸው ከፍተኛ ፋይዳ አላቸው፡፡
ምንም እንኳ አሁንም በከፋ ድህነት ውስጥ የሚቃቀው ህዝባችን ቁጥር ቀላል የሚባል ባይሆንም ባለፉት ሁለት አስር ተከታታይ ዓመታት ሀገራችን ሚሊዮኖችን ከአስከፊ ድህነት ውስጥ ማውጣት ችላለች፡፡ በምግብ እህል ራሳችንን እስከመቻል ደርሰናል፡፡ ትልልቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን በራሳችን ወጪ መገንባት የሚያስችል ሀገራዊ አቅምም ፈጥረናል፡፡ ገፅታችን በውስጥ እየተገነባ ሲመጣ በውጭ ግንኙነት ረገድ ተሰሚነታችን እየጨመረ መጥቷል፡፡ ከምስራቅ ኢስያ ሀገራት ልምድ ተነስተን ስናይ በተለያዩ ምክንያቶች የተሰደደው ዲያስፖራ ወደ ሀገሩ ተመልሶ የለውጥ አካል መሆን መቻሉም አንዱ የህዳሴያችን ምልክት ተደርጎ ይወሳዳል፡፡ 
እነዚህና የመሳሰሉት ማሳያዎችን ስንመለከት የሀገራችን የህዳሴ ጉዞ ተጨባጭ በሆነ መልኩ እየታየ፣ እየጎመራ፣ ወይም በተስፋ ሰጪ ምህዋር ውስጥ የሚገኝ መሆኑን ነው፡፡    

Monday, 24 August 2015

የኢትዮጵያ ወጣቶችና የመሰረታዊ ለውጥ ትግላቸው part 2

በማስከተልም ዋለልኝ ህዝባዊ መንግስት ይመስረት ብሎ ሞገተ። ምን ዓይነት ህዝባዊ መንግስት? በሚለውም ላይ «እውነተኛ ህዝባዊ መንግስት፤ ሁሉም ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች እኩል የሚሳተፉበትና ህዝቦቹ የየራሳቸውን ቋንቋ፣ ባህል፣ ታሪክ የሚጠብቁበትና የሚያሳድጉበት መንግስት ይመስረት» (ዋለልኝ; 1961፤3፡) በማለት ታግሎ መስዋዕት ሆኗል።ዋለልኝን እንደ አብነት ጠቀስን እንጂ በሺዎች የሚቆጠሩ ፊደል ቀመስ የለውጥ ንቅናቄው ግንባር ቀደም ወጣቶች በርካታ ነበሩ፡፡
በ1960ዎቹ የነበረው የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ንቅናቄና በየአካባቢው አርሶ አደሩ ያቀጣጠለው ፀረ-ፊውዳል ንቅናቄ በ1966 የንጉሱን ስልጣን ገረሰሰ፡፡ የህዝቡ ንቅናቄ የፊውዳሉን ስርዓት ቢያስወግድም የአቢዮቱ አንቀሳቃሾች በአግባቡ የተደራጁ ስላልነበሩ በወቅቱ የተደራጀ አቅም የነበረው ወታደራዊ ስርዓት ተቆጣጥሮ የህዝቡን ንቅናቄ ለመጨፍለቅ ሲል ያለምንም ደም ኢትዮጵያ ትቅደም!! ከሚለው አንስቶ ተከታታይ አፋኝ መፈክሮችን ቀርፆ በአስርሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን በቀይ ሽብር ዘመቻ ጨፈጨፈ፡፡ ሠላማዊ ትግል ለውጥ እንደማያመጣ የተገነዘቡት የለውጥ ኃይሎች በብሄራዊም ሆነ በህብረ-ብሔራዊ መልክ ትግላቸውን አቀጣጠሉ፡፡በትግል መስመር ጥራትና በአፈፃፀም ቁርጠኝነት ስርዓቱን ተቃውመው የተንቀሳቀሱ ሁሉ ለፀረ-ደርግ ትግሉ እኩል አስተዋጽኦ ነበራቸው ለማለት ያስቸግራል፡፡ ሆኖም ከተቃውሞ ጀምሮ እስከ ለየለየት የጦር ሜዳ ውጊያ በማምራት 17 ዓመትን በወሰደ ከባድ መስዋዕትነት ለዘመናት በህዝቦች ጫንቃ ላይ ተንጠላጥሎ የኖረው የፊውዳልና ቅሪት ፊውዳል እንዲሁም አምባገነኑ የደርግ ስርዓት እስከ አፈና መዋቅሩ ፈራረሰ፡፡ በዚህም የኢትዮጵያ ህዝቦች መሰረታዊ የልማት፣ የዴሞክራሲና ዘላቂነት ያለው ሠላምን ለማረጋገጥ የተደረገው ስር ነቀል አብዮታዊ ፍልሚያ የመጀመሪያው ምዕራፍ በህዝቦች ንቁ ተሳትፎ በድል ተጠናቀቀ፡፡ የዚህ የጦር ሜዳ ፍልሚያና ክቡር መስዋዕትነት እንዲሁም ድል ግንባር ቀደም ተዋናኝ የያኔ ዘመን ወጣቶች የዛሬ አንጋፋዎች ድርሻ ከፍተኛ ነበር፡፡
ግንቦት 20/ 1983 ዓ.ም የተገኘው ህዝባዊ ድል የዘመናት የህዝቦች ተጋድሎ ድል የተቀናጀበት የአብዮቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ እንጂ የመጨረሻ አልነበረም፡፡ የህዝቦች ትግል ወደ ኋላ ሳይል አስተማማኝ መሰረት የሚይዘው ህዝቦች አንግበዋቸው ለተነሷቸው የሠላም፣ የዴሞክራሲና የልማት ጥያቄዎች ህጋዊ ዋስትና የሚሰጥ ልማታዊና ዴሞክራሲያዊ ህገ-መንግስት በህዝቦች ተሳትፎ መረቀቅና መጽደቅ ነበረበት፡፡ ይህ የመሰረታዊ ለውጥ ንቅናቄው ሁለተኛው ቁልፍ ምዕራፍ ነበር፡፡ ህዝባዊና ቀጣይነት ያለው ህገ-መንግስት አርቅቆና በህዝብ የነቃ ተሳትፎ በማጽደቅ ወደ ዘላቂ ሠላም፣ ልማትና ዴሞክራሲ ጉዞ ለማምራት ሁሉም ያገባናል ባዮች በሂደቱ፣ ከመነሻ እስከ መዳረሻው ሊሳተፉ ይገባ ነበር፡፡ በመሆኑም በኢህአዴግ የሚመራው ጊዜያዊ መንግስት የነበረውን ስርዓት “አስወግጃለሁ፤ ስልጣን ይገባኛል” ሳይል አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ አሉ የሚባሉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች እና ተሰሚነት ያላቸው ግለሰቦች ጭምር የተሳተፉበት የሽግግር መንግስት ተመሰረተ:: በዚህ ጊዜ ውስጥ ለዘመናት ተንሰራፍቶ የቆየውን ህገ-ወጥነት በማጽዳት፣ ለሠላምና መረጋጋት እንዲሁም ለህዝብ ነፃና የተመቸ እንቅስቃሴ እንቅፋት የነበሩ ህገ ወጦችና ሽፍቶች ህዝቡን ባሳተፈ መልኩ በህግ ስር እንዲውሉ ህዝቡ በሠላማዊ መልኩ በነፃነት እንዲንቀሳቀስ ሰፊ ስራ ተከናወነ፡፡ በሽግግር መንግስቱ አማካኝነት የህገ-መንግስት አርቃቂ ኮሚሽን ተዋቀረ፡፡ ኮሚሽኑ ባዘጋጀው መነሻ ሃሳብ ላይ ከ16 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ህዝቦች በረቂቅ ሰነዱ ተወያይተው ማስተካከያና ማሻሻያ ሃሳብ ካቀረቡ በኋላ ወኪሎቹ የበለጠ ተወያይተው እንዲያፀድቁለት፣ በዴሞክራሲያዊ ምርጫ ወኪሎችን መርጦ በተወካዮች አማካኝነት ቀናትን በወሰደ ውይይት ልማታዊና ዴሞክራሲያዊ ህገ-መንግስት ህዳር 1987 ፀደቀ፡፡ ከላይ የተጠቀሱት ስኬታማ ተግባራት የተከናወኑ በዛን ዘመን የነበሩ ወጣቶችና የአሁን ዘመን ጎልማሶች ግንባር ቀደም ተዋናኝነት ነበር፡፡
ህገ-መንግስቱ ከሠላም አኳያ በአገራችን አስተማማኝና ዘላቂ ሠላም የሚረጋገጥባቸው አንቀፆች አስቀምጧል፡፡ የህዝቦች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብት እንዲከበር፣ የዘመናት የግጭት አንድ ምክንያት ሆኖ የቆየው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች የራስን እድል በራስ የመወሰን መብት እስከመገንጠል እውቅና ሰጠ፡፡ በመሆኑም ከብዙዎቹ የዴሞክራሲ ስርዓትን ከሚያራምዱ አገሮች በተለየና በአደገ መልኩ የግለሰብና የቡድን መብቶቻችንን አጣምሮ የሚያከብር የዴሞክራሲ አይነትን የሚፈቅድ ህገ-መንግስት ባለቤት ሆንን፡፡ በብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች የሚገለፀው የቡድን መብት ብቻ ሳይሆን የሃይማኖትና የፆታ እኩልነቶችም ሕገ-መንግስታዊ ዋስትና አግተዋቷል፡፡ ከኢኮኖሚ ልማት አኳያ የዜጎች አንጡራ ሀብት ጉልበት ማንም ሌላ ኃይል በማያዝበት ሁኔታ የዜጎች አንጡራ ሀብት ማለትም ሆነ፡፡ መሬት የጋራ የተፈጥሮ ፀጋ በመሆኑ በመንግስትና በህዝብ እጅ ሆኖ ዜጎች አልምተው ሊጠቀሙበት
6
ተደነገገ፡፡ ይህም የኢኮኖሚና የፖለቲካ ፍትሃዊነትን ያሰፈነ ውሳኔ ነው፡፡ በነዚህ ስኬታማ ተግባራት የያኔ ዘመን ታጋይ ወጣቶች ህዝባቸውን በማንቃትና በማደራጀት የመሪነት ድርሻቸውን ተወጥተዋል፡፡
በማህበራዊ ለልማት መስክ የፆታና የአካባቢ እንዲሁም የብሔር ልዩነቶች ሌሎች አድሎ የሚፈጥሩ ቅድመ ሁኔታዎች ሳይኖሩ ሁሉም እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ዜጎችን የመማር መብት የሚያስከብር ሆነ፡፡ የትምህርት ፍትሃዊነት በቦታ (በከተማና በገጠር) ተደራሽ መሆን ብቻ ሳይሆን በፆታ፣ በብሔርና ብሔረሰብ ፍትሃዊነቱ መረጋገጥ ያለበት መሆኑ በህገ-መንግስቱ በግልጽ ተመላክቷል፡፡ ከዴሞክራሲ ስርዓት አኳያ ስልጣን በህዝብ ይሁንታ እንጅ ከህዝብ ይሁንታ ውጭ ፈጽሞ የማይፈይድ መሆኑ በግልጽ ተመላከተ፡፡ ወጣቶች ሂደቱን በመምራትና ህዝቡን በማደራጀት ታሪካዊ ተልዕኳቸውን በብቃት ተወጥተዋል፡፡
በጥቅሉ መሰረታዊ የህዝብ መብቶችንና ጥቅሞችን በልማታዊና ዴሞክራሲያዊ አግባብ ለሚያረጋግጡ የህዝብ ጥያቄዎች በተሟላና ዘላቂነት ባለው መልኩ መልስ ሰጥቷል፡፡ የፌዴራሉን ህገ-መንግስት ተከትሎ የአማራ ክልልም የራሱን ህገ-መንግስት በምክር ቤቱ አፀደቀ፤ በክልሉ የሚገኙ ብሔረሰቦችም በሚኖሩበት መልክዓ ምድር የራሳቸውን ምክር ቤት አደራጅተው ራስን በራስ የማስተዳደር መብታቸውን ተጎናፀፉ፡፡ ለዘላቂ ሠላማችንና ለአብሮነታችን ዋስትናና ወሳኝ ቅድመ ሁኔታ የሆነው ህገ-መንግስት ፀድቆ ተግባራዊ መሆኑ፣ የኢትዮጵያን ልማታዊ ዴሞክራሲያዊ አብዮት ሁለተኛ ምዕራፍ ያበሰረ ትልቅ ድል ነው፡፡ በዚህ ረገድ የአማራ ክልል ወጣቶች ከአገራችን ወጣቶች ጋር ጣምራ ትግልና ድል ተጎናፅፈዋል፡፡
የአገራችን አብዮት ሦስተኛው ምዕራፍ በልማታዊ ዴሞክራሲያዊ ጎዳና፣ በህዝብ ይሁንታ ላይ የተመሰረተን ህዝባዊ መንግስት መስርቶና ዘላቂ ሠላምን አረጋግጦ፣ በመሰረተ ሰፊና በአደገ ገጽታ ስራ ላይ የዋለ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ፤ ፈጣን፣ ፍትሃዊ እንዲሁም ህዝቡ በየደረጃው ተጠቃሚ የሚሆንበትን የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማትን በቀጣይነት ማረጋገጥ ይጠይቃል፡፡
1.1.3 የህዝባዊ መንግስት ምስረታና የሠላም፣ ልማትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ውጤቶች
የኢትዮጵያ የመሰረታዊ ለውጥ ንቅናቄ ሦስተኛውና ረጅሙ ምዕራፍ ከ1988 ዓ.ም አንስቶ ቀጠለ፡፡ በዚህ ምዕራፍም የወጣቶች ግንባር ቀደም ንቅናቄ ሌላ መተኪያ አልነበረውም፡፡
ሀ/ አስተማማኝና ዘላቂ ሠላምን የማረጋገጥ ትግልና ውጤቶቹ
ድርጅታችን ብአዴን-ኢህአዴግና በሱ የሚመራው ልማታዊና ዴሞክራሲያዊ መንግስታችን ከሽግግር መንግስት ወቅት አንስቶ በትኩረት የያዘውን የሠላምና የመረጋጋት ተግባራት ቀጣይነት ለማስጠበቅ በትጋት ተንቀሳቅሷል፡፡ ለዘመናት ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ ህገ-ወጦችና፣ ጉልበተኞች የአቅመ ደካሞችን ሀብትና ንብረት እንዲሁም ህይወት እንደፈለጉ አደጋ ላይ እየጣሉ ያሻቸውን እያደረጉ የማይጠየቁበት፣ አልፎ አልፎም የሽፍትነትን ስራ በተከታታይ በማከናወናቸው በደጋፊዎቻቸው የሚሞካሹበት ነባራዊ ሁኔታ ነበር፡፡
ብአዴን-ኢህአዴግ ህዝቡን በማንቃት እና በማደራጀት ህገ-ወጥነትን ጉልበተኛነትን፣ በሌላው ላብና ጉልበት ተንጠልጥሎ የመኖርን መጥፎ አባዜ ለመግታት ከፍተኛ ጥረት አድርጓል፡፡ በአንድ በኩል ከደርግ ድምሰሳ ጋር ተያይዞ ተበትኖ የነበረውን በመቶ ሺዎች የሚቆጠር ወታደርና የጦር መሳሪያ በአግባቡ በመሰብሰብ ወታደሩን የሠላምና የተሃድሶ ትምህርት በመስጠትና በማስተማር ወደ ምርት ስራ እንዲገባ አቅም የፈቀደውን በማመቻቸት፣ የተበተነውን የጦር መሳሪያ በመልቀም ህዝባዊ ሚሊሻንና ፖሊስን አሰልጥኖ በማስታጠቁ ሠላማዊነትና ህጋዊነት እንዲረጋገጥ ከፍተኛ ጥረት አድርጓል፡፡ በዚህ ረገድ ወጣቶች ለህይወታቸው ሳይሰስቱ የህዝባቸውን አስተማማኝ ሰላምና ፀጥታ ለማስከበር ተንቀሳቅሰው በከፈሉት አኩሪ መስዋዕትነት የህዝባቸውን ሰላም አስተማማኝና ዘላቂ ማድረግ ችለዋል፡፡
ከመደበኛ የማምረት ተግባሩ ሳይነጠል የአካባቢውን ሠላም የሚጠበቅ ህዝባዊ ሚሊሻን በህዝብ ተሳትፎ በመመልመል እና በማሰልጠን እንዲሁም ቀጣይነት ያለው የአቅም ግንባታ በማድረግ ከህዝቡ የተደተራጀ እንቅስቃሴ ጋር በመሆን የሠላሙ ጉዞ በአስተማማኝ ሁኔታ እንዲዘልቅ ገንቢ ሚና ተጫውቷል፡፡ በፀረ-ዴሞክራሲ አምሳያ የተቀረፀውን የቀድሞ ፖሊስ የተሀድሶ ትምህርት ከመስጠት በተጨማሪ አዳዲስ የፖሊስ አባላት በህዝብ ተሳትፎ ተመልምለው፣ ህዝባዊ ሥነ-ምግባር የተላበሱ ሆነው ህዝብን እንዲያገለግሉ፣ የፖሊስ ኃይሉ ማዕከላዊ ስራ ወንጀል ከመፈፀሙ በፊት መከላከል እንዲሆን፣ ለዘላቂ ወንጀል መከላከል ሰፊ መሰረት ያለው ደግሞ ማህበረሰባዊ የፖሊስ እንቅስቃሴ (Community Pollicing) በዝርዝር የአፈፃጸም ስርዓት ተደራጅቶ ከከተማ እስከ ገጠር ህብረተሰቡ ከፖሊስ ጋር ተደራጅቶ ሰላምን አስተማማኝ የማድረግ ብቻ ሳይሆን ለዘላቂ ሠላም ቁልፍ ተፈላጊነት ያለው የአካባቢ ልማት እንዲረጋገጥ የበኩሉን አወንታዊ አስተዋጽኦ በማበርከት ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ ተግባር የወጣቶች ተሳትፎ ቀጥተኛና ተኪ ያልነበረው ነበር፡፡
ህዝባዊ ፖሊስና ሚሊሻ ከዋናው ባለቤት ከህዝቡ ጋር በመሆን በየደረጃው ከሚገኘው የአስተዳደር መዋቅር ቀጥተኛ አመራር እያገኘ ሠላም በራሱ ምርት እንዲሆን ዜጎች በነፃነት በፈለጉት ጊዜ፣ ከቦታ ቦታ ተዘዋውረው ኑሯቸውን ለማሻሻል እንዲተጉ፣ የሀብትና ንብረታቸው ከለላና ጠበቃ እንዲኖረው መሰረተ ሰፊና ቀጣይነት ያለው ስራ ተሰርቷል፡፡ ከወንጀል መከላከል አልፈው የሚፈፀሙ ወንጀሎችን አጣርቶ ለህግ በማቅረብ እና በማስቀጣት እንደ ሁሉም ተግባራቶቻችን ሁሉ የአፈፃጸም ድክመት ያለበት ቢሆንም ወሳኝ ገጽታው ወንጀለኞች ወንጀል ፈፅመው ከተጠያቂነት እንደማያመልጡ የሚያረጋግጡ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ በአጠቃላይ ባለፉት 24 ዓመታት ሠላም በራሱና ከሌሎች የዴሞክራሲና የልማት ተግባራት ጋር በድምር ተመጋግበው እንዲያድጉ በዚሁ ሂደትም ህዝባችን የሠላም አየር እንዲተነፍስ፣ ሠላማዊና የሰከነ ሁኔታም እንዲረጋገጥ ብአዴንና ህዝቡ አኩሪ ተግባራትን ፈፅመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ወጣቶችና የመሰረታዊ ለውጥ ትግላቸው part 1

ቅድመ 1983 ዓ.ም የነበረው የፖለቲካ ኢኮኖሚ ሁኔታ በጥቂቱ

ኢትዮጵያ ጥንታዊ አገር ናት፡፡ የአፅመ ቅሪቶችና የሌሎች ማጣቀሻዎች ሳይጨመሩ እስከ አሁን የተደረጉ ጥናቶችንና ስምምነት የተደረሰባቸውን ታሪካዊ ማጣቀሻዎች ብቻ ብንወስድ አገራችንና ህዝቦቿ ከ3 ሺህ ዓመት በላይ ታሪክ ያላቸው ናቸው፡፡ የአገራችን ህዝቦች ጥንታዊ ብቻ ሳይሆኑ ቀድመው ስልጣኔ ከጀመሩ ጥቂት የዓለም አገራት ህዝቦች ተርታ የምንመደብ እንደሆንንም ብዙ የውጭ አገር ምሁራን ሳይቀሩ ያረጋገጡት ጉዳይ ነው፡፡ በምስራቅ አፍሪካ ከእንጨት ቴክኖሎጂ ቀድሞ ከመጀመሩ ጋር ተያይዞ የእርሻ ቴክኖሎጂ በክልላችንም ሆነ በአገራችን ቀድሞ እንደተጀመረ ምርምሮች ያረጋግጣሉ፡፡ ቢያንስ ቢያንስ ጤፍንና ቡናን ለዓለም ገፀበረከት ማቅረባችን ለማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ እንስሳትን በማላመድ ጥቅም ላይ ካዋሉ ህዝቦች ተርታም እንደምንመደብ የተረጋገጠ ነው፡፡ በጥቅሉ በግብርናው መስክ ቀድመው ከጀመሩት እንመደባለን፡፡
በግብርና ቴክኖሎጂ ብቻ ሳይወሰን በኪነ-ህንፃ ጥበብም ከግሪክ፣ ከአረቢያና ከአንዳንድ የህንድ አካባቢዎች የሚመጣጠን የዘመናዊ ህንፃ ጥበብን ቀድመን እንደጀመርን አሁን ድረስ ያሉ አሻራዎች ህያው ምስክሮች ናቸው፡፡ የአክሱም፣ የላሊበላ፣ የጎንደር ፣ የሐረር ጀጎል ግንብ፣ በደቡብ የጥያ ትክል ድንጋይ የመሳሰሉት ለዚህ ዋቢ ማሳያዎች ናቸው፡፡ ክልላችንም ሆነ አገራችን ከላይ በተጠቀሱት ሳይወሰኑ የኃይማኖት ብዝሃነትና የቋንቋ ብዝሃነት በሰፈነበት ነባራዊ ሁኔታም ገዥዎቹ እየቆሰቆሱ ከፈጠሩት ግጭት ባሻገር ህዝቦቿ በመግባባትና በመቻቻል ለፍትሀዊ ጥቅም በአብሮነት መኖር ዋና መገለጫቸው ነው፡፡ የራሳችን ፊደል ያለን ከመሆናችንም በላይ በጥበበ ቃላት ግንባታ መነሻ አቅም ነበረን፤ ይህ ደግሞ ለሳይንስና ቴክኖሎጅ እድገት የራሱ አቅም ሊኖረው የሚችል ነበር፡፡ በራሳችን ታሪክ፣ ቋንቋ፣ ባህል እና እሴት እንዲሁም ሥነ-ልቦና የምንኮራና የውጭ ጠላትን ተደጋጋሚ እና ተከታታይ የጥቃት ሙከራ ተባብሮ በመመከት ነፃነታችንን አስከብረን የመቆየት አኩሪ ታሪክ ያለን ሲሆን የአማራ ክልል ህዝቦችም ለዚሁ አገራዊ ኩራታችን መጠበቅ የበኩላቸውን አኩሪ ተግባር አከናውነዋል፡፡
በዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ረገድም አስፋፍተንና አዳብረን አገልግሎት ላይ አላዋልነውም እንጂ የኦሮሞ አባገዳ ስርዓት በየ8 ዓመቱ የስልጣን ሽግግር የሚያደርጉበት ሁኔታ ነበር፡፡ ይህን በምርጫ የሚገለፅ የዴሞከራሲ ገጽታ ያለው የስልጣን ሽግግር በጥናትና ምርምር በማዳበር ለላቀ ጥቅም አውለነው ቢሆን ኖሮ በዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታም ቀድመው ከጀመሩት ተርታ መመደብ እንችል ነበር፡፡ ሆኖም በአግባቡ ቀምረን ስራ ላይ ሳናውለው ቆይተናል፡፡
እነዚህ የስልጣኔ አሻራዎች ከ15ኛው ክፍለ ዘመን ወዲህ አንስቶ እየተሸረሸሩ በመምጣታቸው ድህነትና ኋላቀርነት፣ግጭትና ደም መፋሰስ፣ አለመግባባትና መናቆር እየተከማመሩ ሂደው የማታ ማታ ከ1950ዎቹ እስከ 1980ዎቹ መጀመሪያ እንደ አገር በጋራ የማንቀጥልበት ሁኔታ አንዣብቦ ነበር፡፡ ትልቅ ከነበርንበት ወደ
2
አልተቋረጠ የቁልቁለት ጉዞ ሲያንሸራትቱን የነበሩት ችግሮች ምንድን ናቸው? ብለን ስንመረምር ፊት ለፊት የሚታዩት የብሔሮችና፣ የብሔረሰቦችና የህዝቦች ብዝሃነትንና እኩልነትን የሚያከብር ሁኔታ አለመኖሩ፤ የሃይማኖት እኩልነት አለመከበር፤ የእድገትና ብልፅግና መሰረት የሆኑት መሬት፣ ጉልበት፣ እውቀት እና የካፒታል አቅም በጥቂቶች እጅ ገብቶ ብዙሃኑ የበይ ተመልካች መሆኑ በንድፈ ሃሳብም ሆነ በተግባር ተረጋግጦ ያደረ እውነት ሆነ፡፡
በእኛም አገር ሆነ በሌሎች አገሮች የተደረጉ ጥናቶችና ተግባራዊ ተሞክሮዎች ቀድመው ያደጉ አገሮች የሚያረጋግጡት የእድገታቸው ሚስጥር በህዝባቸው ዘንድ የተሳካ የህግ የበላይነት መረጋገጡ፣ የዜጎች ሀብት የማፍራትና የሀብትና የንብረት ባለቤትነት በአስተማማኝ ሁኔታ መከበሩ፣ የገዥዎች /በስልጣን ላይ ያሉ ስርዓቶች/ ስልጣን የተገደበ መሆን፣ ምንም እንኳ በየአገሩ የነበሩ ኋላቀርና ፀረ-ዴሞክራሲ አገዛዞች ህዝብን ከመበዝበዝና ከመጫን ወደ ኋላ ያሉበት ጊዜ ባይኖርም ቀድመው መለወጥ የቻሉ አገሮች መነሻ ምክንያቱ ስርዓቱ በህግ በተደነገገ የስልጣን ክፍፍል ውስጥ ህዝብ ላይ የሚያሳድረው ጫና በተወሰነ ደረጃም ቢሆን በህግ የተገደበ መሆኑ፣ ዜጎች አንፃራዊ ነፃነት አግኝተው የግላቸውን፣ የቤተሰቦቻቸውንና የጋራ ልማታቸውን እንዲያፋጥኑና በዚህ ሂደት አማካኝነት የአካባቢና የአገር እድገትም እንዲፋጠን አግዟል፡፡
በእኛ አገር ለዘመናት የቆዩ ስርዓቶች ስልጣናቸው በአግባቡ የተገደበና በታወቀ የህግ አግባብም የሚመሩ አልነበሩም፡፡ እስከ 1970ዎቹ መጨረሻ የነበሩ ስርዓቶች አርሶ አደሮች ያለምንም እገዛ በራሳቸው ጥረት ያመረቱትን ምርት ለገዥዎቹ ይሰፍራሉ፤ የገዛ በሬዎቻቸውንና የእርሻ መሳሪያዎቻቸውን ይዘው ለገዢዎች ያገለግላሉ፤ ደክመውና ጥረው ግረው ያመረቱትን የስርዓቱ ባለስልጣናትን ወታደሮች ይቀሟቸዋል፡፡ በአሰኘው ጊዜ የፈለገውን አይነት መዋጮ ይሰበስባል፡፡
በ1848 ዓ/ም ሰሜን ኢትዮጵያን ለመጎብኘት የመጣና የነበረውን በፍዳና በስቃይ የተሞላውን የአርሶ አደሩን ህይወት በአንክሮ ተመልክቶ የታዘበውን ዋልተር ፕላውደን የተባለ እንግሊዛዊን ጠቅሶ እንደዘገበው «…አርሶ አደሮች ከምርታቸው… ለሹም ይሰፍራሉ፡፡… የገዛ በሬዎቻቸውን ጠምደው የንጉሱንና የአገር ገዥውን መሬት ያርሳሉ። …አባወራው በራሱ ኪሳራ የተወሰኑ ቁጥሮች ያሏቸውን ወታደሮች ይቀልባል። አገር ገዥው በሬ፣ በግ፣ ፍየል፣ ቅቤ፣ ማርና ሌሎች የሚያስፈልጉትን ነገሮች የመውሰድ መብት አለው። ገዥው ከሚገዛቸው አርሶ አደሮች …ባሻው ጊዜ ከእያንዳንዱ አርሶ አደር መዋጮ ይቀበላል።» (የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ... ፤17)
በአማራ ክልልም ሆነ በአገራችን የነበሩ ስርዓቶች የህዝብን ሠላምንና ደህንነትን ጠብቀው በተረጋጋ መልኩ ወደ ልማትና እድገት እንዲረማመዱ የሚያግዙ ሳይሆኑ የላቀ ስልጣን ጨብጠው የአብዛኛዎቹን ህዝቦች ሀብትና ንብረት ለመምጠጥ ሲሉ በሚቆሰቁሱት ጦርነት ህዝቦች ለደህንነታቸው ዋስትና ሳይኖራቸው የኖሩ ናቸው፡፡ ከግብርና ተነስተው ወደ ካፒታል እድገት ለማምራት፣ ከዝቅተኛ እስከ ከፍተኛ የንግድ እንቅስቃሴ መስፋፋት ነበረበት፡፡ ህግና ስርዓት በአስተማማኝ ሁኔታ ባልሰፈነበት፣ ለንግድ እንቅስቃሴ የተመቸ የሰውና የሸቀጥ ዝውውር ማድረግ የሚያስችል ሠላማዊ ሁኔታ ባልሰፈነበት ይህን ማከናወን የሚቻል አልነበረም፡፡ በመሆኑም ያደጉ አገሮች ለእድገታቸው ያገዛቸው እነዚህንጉዳዮች ደረጃ በደረጃ እያሻሻሉ መሄዳቸው ነው፡፡ ከላይ የተጠቀሱት ሁኔታዎች የተመቻቹላቸው ሲሆን በእኛ አገር ደግሞ በተቃራኒው የተመቸ የሠላም፣ የፍትህና የልማት ሁኔታ አልነበረም፡፡
የተጠቀሰው ሁኔታ ዝቅተኛ ምርታማነት ፀንቶ እንዲቆይ ያስገደደ ከመሆኑም በላይ በየወቅቱ እየተፈራረቁ የሚከሰቱ የድርቅ አደጋዎች አርሶ አደሩ ከገዥዎች ምዝበራ ያተረፈውን አንጡራ ሀብት እያደቀቁ ህዝቦቿን ለስቃይና ለሞት ሲዳርጉ ኖረዋል፡፡ የሩቁን ትተን እንኳ ከ1880 እስከ 1980 ለመቶ ዓመት የዘለቀውና ወቅት እየጠበቀ የሚከሰተው ተከታታይ ድርቅና እሱን ተከትሎ የሚስተዋለው ረሃብ በሰውና በእንስሳት ላይ እልቂት የፈጠረበት ሁኔታ እንዳለ ከፊሉን በአይናችን ተመልክተነዋል፡፡ ከላይ የተጠቀሱት ችግሮች ተደምረው በህዝባችን ውስጥ አልችልም ባይነት፣ ተስፋ መቁረጥ፣ ተረጅነትና ጠባቂነት ቀላል ባልሆነ ደረጃ ተንሰራፍተው የቆዩበት ሁኔታ ተስተውሎ ቆይቷል፡፡
በአንድ ወቅት ትልቅ የነበርን ቢሆንም ከላይ ዘርዝረን በጠቀስነው ሁኔታ ከትልቅነት ማማ ቁልቁል ተንሸራተን እንደ ህዝብና እንደ አገር በጋራ ያለመኖር አደጋ አናዣቦብን ነበር፡፡ ሆኖም ይህን አስከፊ ሁኔታ ህዝቦች በተናጠልና በጋራ በመሰላቸው አግባብ ታገሉት እንጂ ዝም ብለው አልተመለከቱም፤ አልተቀበሉትም፡፡ በዚሁ ፀረ-ጭቆናና ብዝበዛ ትግል ውስጥ የትላንት ወጣቶች ትግል ግንባር ቀደምና በትውልድ አኩሪ ንቅናቄ ነበር፡፡
1.1.2 የአገራችን ህዝቦች በተለይም የወጣቶች ተጋድሎ
በአገራችን ለዘመናት እየተፈራረቁ የዘለቁ ስርዓቶች ለህዝብ ሠላም፣ ዴሞክራሲ እና በየደረጃው ተጠቃሚ የሚሆንበትን ስርዓት ለመገንባት ተፈጥሯዊ ሁኔታቸው የማይፈቅድና በመጣጭነት ህዝብን ሲያሰቃዩ የኖሩ በመሆናቸው ህዝቦቹ ከመታገል የቦዘኑበት ሁኔታ እንዳልነበረ ታሪክ ያረጋግጥልናል፡፡ የህዝቦቹ ትግል ያልተደራጀና የተበታተነ ስለነበር በወቅቱ የተደራጀው ፀረ-ዴሞክራሲ ኃይል በቀላሉ ተቆጣጥሮት ዘልቋል፡፡ የሩቁን ትተን ከ1930ዎቹ ጀምሮ እስከ 1980ዎቹ መጀመሪያ ድረስ ጉልህ የሆነ የተደራጀና የተናጠል የህዝቦች ተጋድሎ ተካሂዷል፡፡ በዚህ ውስጥ የወጣቶች ሚና ጉልህ ነበር፡፡
የህዝቡ ተጋድሎ በአጠቃላይ በተለይም ደግሞ የወጣቶች ግንባር ቀደም ንቅናቄ የኢትዮጵያን ንጉሳዊ አገዛዝ ስልጣንን ቀይረው የሚፈልጉትን ልማታዊና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት በወቅቱ መገንባት ባይችሉም ከኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ ጋር የተቃኘ የአንገዛም ባይነት ትግል አካሂደዋል። በአማራ ክልል ሁኔታም በ1930ቹ የተካሄደው የጎጃም ገበሬዎች አመጽ፣ በተለያዩ አካባቢዎች የተካሄዱ የአርሶ አደሮችና የየአካባቢው ፊውዳሎች ፍጥጫና የ1964/5 የወሎ ረሃብን ተከትሎ የተቀሰቀሰው ህዝባዊ አመጽ ወዘተ… የሚጠቀሱ ናቸው።
የአማራ ክልል ህዝቦችን ጨምሮ የኢትዮጵያ ህዝቦች ፀረ-ብዝበዛና ፀረ-ጭቆና ተጋድሎ ትምህርት ቀመስ በሆነው ኃይል ድጋፍ ማግኘት የጀመረው ከ1950ቹ ወዲህ ነው። በአቤ ጎበኛ እንደተጻፈ ጠቅሶ የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ባሳተመው የአማራ የባህልና ኪነ-ጥበብ መጽሐፍ እንደተጠቀሰው፣
«ተረግጦ ተገፍቶ፤
አልቅሶ ተጠቅቶ፣
ተርቦ ተጠምቶ።
በድንቁርናና በህመም በስቃይ በረሀብ በችግር፣
እየተንገላቱ ዘላለም ከመኖር፣
ከእኩልነትና ከነጻነት ጋር ይሻላል መቃብር።
እንኳን ከውርደት ጋር እንኳን ከችግር ጋር ከደዌ፣ ከጥቃት፣
ከክብርም ጋር ቢሆን ከብዙ ጌትነት፣
ኑሮ ጣዕም የለውም ከሌለው ነጻነት።»
(ባህልና ቱሪዝም ቢሮ; 2001፤ 169)
በዚህ መልክ እየተቀነቀኑ የየህብረተሰብ ክፍሉን የሚያነሳሱ ጽሑፎችና አስተያየቶች መውጣት ጀመሩ። በ1960ቹ ህዝባዊ ትግሉን የተማሪዎች ንቅናቄ የበለጠ ወደ ላቀ ደረጃ አሳደገው። ነባራዊው የህዝቦች መደባዊና ብሔራዊ ጭቆና በድፍረት የተገለጠው ከአማራ ህዝቦች አብራክ በወጣውና የተማሪዎች ንቅናቄ አባልና ግንባር ቀደም መሪ በነበረው የያኔው ዘመን ወጣት ዋለልኝ መኮንን ሲሆን በወቅቱ የሚከተለውን ጽፏል።