Monday, 11 January 2016

በግድባችን ያልታዩ እጆች የሉም! አሉላ ወርቁ



ህዳር 16 ረፋድ ላይ ነበር የአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ወደ ዝግጅት ክፍላችን የላከው የሚዲያ ሽፋን ደብዳቤ በእጄ የገባውና መመደቤን ያወኩት፡፡ አላማውም ወደ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መሆኑ ደግሞ አስፈነደቀኝ፡፡ በደብዳቤው እንዲህ የሚል ጎልቶ ይነበባል፡፡ “2ኛው ዙር የኪነ ጥበብ ለህዳሴ ጉዞ” እነሆ በእለቱ የመሄድ አጋጣሚውን ማግኘቴ አስደስቶኝ ከቢሮ የሚያስፈልጉኝን ግብአቶች በመያዝ ወደ ቤት አቅንቼ ለጉዞዬ ስሰናዳ በእለቱ ይተላለፍ የነበረ የምሽት ዜና ትኩረቴን ሳበው፡፡
ዜናው የሻሸመኔ ከተማ ነዋሪ ወ/ሮ አሰለፈች ፀጋዬ የ33 ሺህ ብር ቦንድ መግዛታቸውን ያትት ነበር፡፡ ወይዘሮዋ የግድቡ ስራ ከጀመረ ከ2003 ጀምሮ በ1 ሺህ ብር ቦንድ ግዥ የጀመሩት ድጋፍ ዛሬ ላይ በችርቻሮ ንግድ ተሰማርተው በሚያገኙት ገቢ የ33 ሺህ ብር ቦንድ ለመግዛት መብቃታቸውን ለኢብኮ ጋዜጠኛ ያስረዳሉ፡፡

ዘርፈ ብዙው የእፅዋት ማእከል!




ማዕከል የማቋቋም ስራ የተጀመረው እ.ኤ.አ በ1543 በጣሊያን ሀገር ነው፡፡ ጣልያን ሀገር የሚገኙ የፓድዎና የፒሳና ማዕከላት በእፅዋት ማዕከል ታሪክ አንጋፋ እንደሆኑ የተለያዩ ጥናቶቹ ያመላክታሉ፡፡ በእፅዋት ስብስቡና በሳይንሳዊ ይዞታው ተወዳዳሪ የማይገኝለት ግን እ.ኤ.አ በ1759 የተቋቋመው የእንግሊዙ ሮያል ኪው እጽዋት ማዕከል ነው፡፡
በአፍሪካም ዘመናዊ የእጽዋት ማዕከላት በ20ኛው ክፍለ ዘመን ማግስት እ.ኤ.አ በ1913 መቋቋም እንደጀመሩ ድርሳናት ያስረዳሉ፡፡ በአፍሪካ የእፅዋት ማዕከል ቀዳሚውና እድሜ ጠገቡ የደቡብ አፍሪካው ክሪስታን ቡሽ ብሔራዊ የእጽዋት ማዕከል ነው፡፡
ዘመናዊ የእጽዋት ማዕከላት እጽዋቶቹን ከመጥፋት አደጋና ስጋት በመከላከል ለምርምር፤ ለትምህርትና ለኢኮ ቱሪዝም ትልቅ አስተዋጽኦ ያበረክታሉ፡፡ ዛሬ ላይ ከ130 የሚበልጡ ሀገራት የእጽዋት ማዕከላትን ጥቅም ጠንቅቀው በመረዳታቸው ከ2 ሺህ 500 በላይ መሠል የእጽዋት ማዕከላትን አቋቁመው ለመጥፋት የተቃረቡ እጽዋትን በማራባት ለአረንጓዴው ልማት መቀጣጠል የበኩላቸውን ድርሻ እየተወጡ ይገኛሉ፡፡