የግንቦት 20 25ኛ ዓመት የድል በዓልን ምክንያት በማድረግ ባዘጋጀነው ልዩ ዕትም ጋዜጣ የግንቦት 20 እንግዳ
አድርገን ያነጋገርናቸው የአዲስ አበባ ኢህአዴግ ኮሚቴ ጽ/ቤት ሃላፊ
አቶ ተወልደ ገ/ ፃድቃን ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተውናል፡፡ መልካም ንባብ፡፡
ህዳሴ፡- አስከፊውን የደርግ ስርዓት ለማስወገድ የተከፈለው መራራ መስዋዕትነት እንዴት ይገልፁታል?
አቶ ተወልደ፡- ሁሉም እንደሚያውቀው ቀደም ብሎ መላው የሀገራችን ህዝቦች በአስከፊ የጭቆና ስርዓት ሲማቅቁ
እንደነበር ይታወቃል፡፡ እንደ አንድ ሀገር ከተመሰረተች በኋላ የተለያዩ የፊውዳል ስርዓቶች እየተፈራረቁ በህዝቡ ላይ ብሄራዊና መደባዊ
ጭቆና ሲያደርሱበት ኖረዋል፡፡ ይህንን ጭቆና ለመቅረፍ በተለያዩ አካባቢዎች የተለያዩ ትግሎችን ሲያካሄዱ የቆዩ ሲሆን በርካታ የአርሶ
አደሮች የአመፅ እንቅስቃሴዎች ነበሩ፡፡ ቀጥሎም በ1960ዎቹ አካባቢ የሀይለ ስላሴን ስርዓት ለመገርሰስ ወይም ለመውደቅ ምክንያት
የሆነው የከተማው ተማሪ፣ ላብ አደር ባጠቃላይ አርሶ አደሩ በሙሉ ፀረ ብሄራዊና መደባዊ ጭቆና ላይ ሰፊ ትግል አካሄደዋል፡፡
ለፆታ እኩልነት፣ ለፍትህ፣ ለብሄር ብሄረሰቦች እኩልነት በተለይ የተማሪዎች ንቅናቄ ሰፊ ትግል ሲያደርጉ ቆይተዋል”” በተለያየ መንገድ ማለት ነው፡፡ ነገር
ግን ትግሉ የተደራጀ ስላልነበር በህዝብ እንቅስቃሴና ንቅናቄ የሀይለ ስላሴ ስርዓት ሲወድቅ በወቅቱ የተደራጀ የደርግ ሀይል ስለነበር
ህዝቡን ነጥቆ ስልጣን ላይ ወጣ፡፡ ህዝቡን የደርግ ወታደር ሀይሉን ከቀማው በኋላ ከትጥቅ ትግል ውጭ ስልጣኑን በሰላማዊ መንገድ
ሊያስረክብ እንደማይችል ታመነበት፡፡ በወቅቱ የነበሩ የተማሪዎች ንቅናቄ አመራሮች ይህንን ሲያውቁ የተለያዩ አደረጃጀቶችን መፍጠር
ጀመሩ፡፡ ስልጣን የሰፊው ህዝብ መሆን እንደማይችል ካረጋገጡ በኋላ ወደ ትጥቅ ትግል ገቡ፡፡
ከዛ በኋላ ግን በ1967 ዓ.ም የአሁኑ ኢህአዴግ በህወሓት አማካኝነት ወደ በረሀ ወጥቶ የትጥቅ ትግሉ ጀመረ፡፡
ቀጥሎም በቅደም ተከተል የቀድሞው ኢህዴን/ብአዴን፣ ኦህዴድ፣ ደኢህዴን እያለ ለ17 ዓመታት ያህል ብሄር ብሄረሰቦች መብታቸው እንዲከበር፣
ዴሞክራሲ በሀገሪቷ እንዲረጋገጥ፣ ፍትህ እንዲሰፍን፣ ለሰላም ለልማት ለእኩልነት ብለው መራራ ትግል አካሄደዋል፡፡
የትጥቅ ትግሉ ታሪክ በአጭር ጊዜ ተወርቶ
የሚያልቅ አይደለም፡፡ በርካታ መራራ የትግል አመታት የታለፈበት ስለሆነ የዚህን ያህል ጊዜ ያስፈልጋል ታሪኩን በደንብ ለመተንተንና
ግንዛቤ ለማስጨበጥ፡፡ በጥቅሉ ግን ከጫፍ እስከ ጫፍ ምንም እንኳ የትጥቅ ትግሉ በአንድ አቅጣጫ ቢጀመርም ህዝቡ በአራቱም አቅጣጫ
ታግሏል፡፡ ለምሳሌ በወቅቱ ህወሓት ወደ ትጥቅ ትግሉ ገብቶ ሲታገል የተለያዩ ብሄር ብሄረሰብ ተወላጆች ከአራቱም አቅጣጫ ተቀላቅለው
አብረውት ሲዋጉ ነበር፡፡ ቀጥሎም ኢህዴን ማለትም የኢትዮeያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ የአሁኑ ብአዴን ሲመጣ የተለያዩ ብሄር ብሄረሰቦችን አካቶ ሲታገል ቆይቷል፡፡
ኦህዴድ ሲፈጠርም ህዝባዊ አድማሱ ሰፋ፡፡ የደቡብ ኢትዮeያ ተወላጆችም አንድ አደረጃጀት ፈጥረው በትጥቅ ትግሉ መጨረሻ ዓመታት ታግለዋል፡፡
ስለዚህ የትጥቅ ትግሉ በጣም መራራ የነበረ
ሲሆን መስዋዕትነትን የሚጠይቅ፣ የታጠቀን ታጋይ ብቻም ሳይሆን አርሶ አደሩ የከተማው ነዋሪ ለአላማው ከፍተኛ መስዋዕትነት የከፈለበት
ሁኔታ ነው የነበረው፡፡ ይህንን መራራ ትግልና ከፍተኛ መስዋዕትነትን ለመክፈል የብሄር ብሄረሰቦች እኩልነት ዴሞክራሲ፣ ሰላም፣ ልማት
እንዳይረጋገጥ ዘግቶ የበነረውን ሀይል ለማስወገድ አስቻለ ማለት ነው፡፡
ህዳሴ፡- ግንቦት 20 የህዳሴአችን መሰረት
ነው ስንል ምን ማለታችን ነው? ይህንንስ በተጨባጭ ተሞክሮ እንዴት ይገልፃል?
አቶ ተወልደ፡- ግንቦት 20 የህዳሴአችን
መሰረት ነው ስንል የትጥቅ ትግሉ የተካሄደበት ዋነኛው ምክንያት ደርግን ለማስወገድ የመጨረሻ አላማ ተደርጎ የተወሰደ አይደለም፡፡
ልማት ለማምጣት፣ ዴሞክራሲያዊት ሀገር ለመመስረት፣ የብሄር ብሄረሰቦች፣ የሴቶች፣ የሀይማኖቶች እኩልነት ለማረጋገጥ ሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ
መብቶችን ለማስከበር፣ እድገት፣ ብልፅግና የህዝቦች ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ መጀመሪያ ይህንን ለማድረግ የሚያስችል ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር
ስለነበር ነው፡፡ ይህን እንዳይደረግ ዘግቶ የያዘን ሀይል መወገድ ስለሚያስፈልግ ብሄር ብሄረሰቦች በአንድነት ተነሱ፡፡
እነዚህን መብቶችና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ
ካልተቻለ ሰላምን ማረጋገጥ አይቻልም፣ ዴሞክራሲያዊ መብት ማስከበር አይቻልም፣ ልማት ለማምጣት መላውን ህዝብ ማስተባበር አይቻልም
በዚህም ምክንያት ከላይ የጠቀስኳቸውን ለማረጋገጥና ህዝቡን በየደረጃው ተጠቃሚ ለማድረግ ዘግቶ ይዞ የነበረን የደርግ ስርዓት በትጥቅ
ትግል ገርስሶ መጣል ያስፈልጋል፡፡ ይህንንም በመፈፀም የትግሉ የመጀመሪያ ምዕራፍ ተጠናቀቀ፣ ሁለተኛው የትግል ምዕራፍ ተበሰረ ማለት
ነው፡፡ የህዳሴ ጉዞ መነሻ ማለት ይህ ነው፡፡
በዚህም ምክንያት ሁለተኛው የትግል ምዕራፍ
የተሀድሶ ጉዟችን መነሻ ነው ብለን እንወስዳለን፡፡ የደርግ የታጠቀን ሀይል ካስወገድን ኢህአዴግ ታግየ ድሉን ያመጣሁ እኔ ነኝና
ስልጣኑን መያዝ ያለብኝእኔ ነኝ አላለም፡፡ በወቅቱ የተለያዩ ፖለቲካ ፓርቲዎች ወደ አንድ ጠረጴዛ መጥተው በአንድ አዳራሽ ውስጥ
እንዲመክሩ አንዲዘክሩ እንዲከራከሩ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ ተፈጠረ፡፡ ይሄም አንዱ የዴሞክራሲያዊ ስርዓት መነሻ ሆኖ ተወሰደ፡፡ የሽግግር
መንግስት ምስረታ ጉባኤ ተካሄደ፣ ከዛ ቀጥሎም ህገ መንግስት ተረቀቀ፣ በህዝብም የነቃ ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎ የህገ መንግስቱ ረቂቅ
በተወካዮቹ እንዲፀድቅ ተደረገ፡፡
ይህ ሁሉ ተግባር ለህዳሴ ጉዟችን የመሰረት
ድንጋይ
4 HÄs¤ የ ግንቦት 20 qN 2008
ነው፡፡ በአሁኑ ሰዓት እየተገበርነው ያለው ስራ በሙሉ በህገ መንግስታችን ማዕቀፍ ስር ሆነን ነው፡፡ ስለዚህ
ይህንን ለማድረግ እንዳንችል በሩን ዘግቶና ቆልፎ የነበረን ሀይል በሩን በርግደን ከፍተን ባናስወግደው ኖሮ ላለፉት 25 አመታት
የተሰሩ ስራዎችና ስናስመዘግባቸው የመጣናቸው ድሎች ሊኖሩ አይችሉም ነበር፡፡ የዚህ ሁሉ ውጤትና የህዳሴ ጉዟችን መነሻ የግንቦት
20 ድል ነው ስንል ለዚህ ነው፡፡
ከዚህ ጋር አያይዘን ነው ግንቦት 20 የብሄሮች የትግል ውጤት ነው የምንለውም፡፡ ምናልባት የብሄር ብሄረሰቦች
የትግል ውጤት ነው ስንል መጀመሪያ ላይ ለማንሳት እንደሞከርኩት አንደኛ በተበታተነና ባልተደራጀ መንገድ ሁሉም የኢትዮeያ ብሄር ብሄረቦች ሲታገሉ ቆይተዋል፡፡ ሁለተኛ ይህ ትግል እንዲጠነሰስ
ምክንያት የሆነ በ60ዎቹ መጀመሪያ የሀይለስላሴን ስርዓት ለማስወገድ መላው የኢትዮeያ ብሄር ብሄረሰቦች በጋራ በገጠርም በከተማም ስርዓቱን አንቀጥቅጠው እንዲገረሰስ
ያደረጉት ትግል መነሻውም ይሄው ነው፡፡ ትግላቸውንም አካሄደው መስፍናዊውን አፋኝ ስርዓት ሲገረስሱ ሌላ ወታደራዊ ሀይል ተተካ፡፡
ይህንንም ስርዓትም ሁሉም ብሄር ብሄረሰቦች በከፈሉት መስዋዕት ተወገደ፡፡
ትግሉ የሁሉም ብሄር ብሄረሰብ ውጤት ነው ሲባል መራራውን የትጥቅ ትግል ከሰሜን ኢትዮeያ ተነስቶ ወደ መሀል ሀገር ሲገሰግስ መላው አርሶ አደር ታጋዩን በደስታ
በመቀበል የሰው ሀይል መልምሎ፣ ስንቅን በማቀበልም ትልቅ አስተዋፅኦ በማበርከት የራሱን ድርሻ ተወጥቷል፡፡ ባጠቃላይ ህዝቡ ትግሉን
ሲመራ የነበረውን ድርጅት ተንከባክቦ ነው እዚህ ደረጃ ላይ በሙሉ ልብ ተቀብሎ ያደረሰው፡፡ ከዚህ ህዝብ አብራክ የፈለቁ የሁሉም
ብሄር ብሄረሰብ ታጋዮች ደግሞ በዚህ ድርጅት ጥላ ስር ሆነው ታግለዋል አላማው ከዳር እንዲደርስም እስከመጨረሻ መስዋዕትነትም ከፍለዋል፡፡
ገና ከመነሻው ጥያቄው የህዝብ ነው ትግሉም የህዝብ ነበር ድሉም የመላው ህዝብ ነው የምንልበት ምክንያትም ጥያቄው
የመላው ኢትዮeያ ህዝብ ስለነበር ነው፡፡ ጥያቄውም እንዲመለስለት ሁሉም ህዝብ በእኩል ስለታገለ ነው፡፡ በየአካባቢው መስዋዕትነትም
ስለከፈለ ነው፡፡
ህዳሴ፡- አዲስ አበባችን ከግንቦት 1983 ዓ.ም በፊት ምን ነበር ያጣችው? ምንስ ትመስል ነበር?
አቶ ተወልደ፡- ሁሉም የሀገራችን ከተሞችና ገጠሩ ክፍል በዴሞክራሲ እጦት ሲማቅቁ ነው የኖሩት፡፡ ከተሞች ሲመሰረቱ
ለልማት፣ ለህዝቦች ተጠቃሚነት፣ የእድገት ማዕከል እንዲሆኑ ታስቦ ሳይሆን ለአስተዳደራዊ ስራዎች ቢሮክራሲውን ለማገልገል ተብለው
የሚፈጠሩ ከተሞች ነበሩ፡፡ የአዲስ አበባ አመሰራረትም ከዚህ የተለየ አይደለም፡፡
በተለይ ከተማችን አዲስ አበባ የሀገሪቷ
ማዕከል እንደመሆኗ መጠን በሁሉም መስክ የመጠቀ እድገት ሊኖራት ይገባ ነበር፡፡ በአደረጃጀቷ፣ ለህዝቡ በምታረጋገጠው ዙሪያ መለስ
መብቶች፣ በመልካም አስተዳደርና ከሁሉም በላይ ልማትና እድገት ለማረጋገጥ የህዝቦቿን ተጠቃሚነትና የኑሮ ሁኔታን ለማሻሻል በሚያስችል
መንገድ ሲሰራ አልቆየም፡፡
ይልቁንም ከተማዋ የቢሮክራሲ መገልገያ
ሆና ወጣቱ እየታነቀ ወደ ማያምንበት ጦርነት የሚማገድባት መማር እንደ ጥፋት የሚወሰድበት፣ ተስፋ የቆረጠ ህዝብ የበዛበት ሁኔታ
ነው የነበረው፡፡
ኢህአዴግ በ1983 አዲስ አበባ ሲገባ
አዲስ አበባ ምን ትመስል ነበር ለተባለው ከተማዋ በጣም የተጎሳቆሉ መኖሪያ ቤቶችና ድሀ ህዝብ የሚኖረባት የድህነት መገለጫ ከተማ
ነው የነበረችው፡፡ ለስሙ ግን ዋና ከተማ ተብላ የምትጠራ እንጂ በየመንደሩ ያረጀ ያፈጀና የተጎሳቆለ መኖሪያ ቤቶች ነው የነበሯት፡፡
አብዛኛውም የከተማዋ ህዝብ በከፍተኛ የድህነት አዝቀት ውስጥ ይማቅቅ የነበረ ሁኔታ ነው የነበረ፡፡ ይህንንም ችግር ለመፍታት ምንም
አይነት ጥረት የማይደረግበት ሁኔታ ነው የነበረው፡፡
ህዳሴ፡- ባለፉት 25 ዓመታት የመጡ ለውጦችስ
እንዴት ይገለፃሉ?
አቶ ተወልደ፡- መንግስት በመሰረተ ልማት፣
በኢኮኖሚ ልማት፣ በዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ የተረጋጋ የኑሮ ሁኔታ በከተማዋ እንዲፈጠረ የቻለውን ሁሉ በማድረግ በአጭር ጊዜ
በርካታ ስራዎችን ሰርቶ ውጤት ማስመዝገብ ችሏል፡፡ ለምሳሌ ከዴሞክራሲ አንፃር ስናይ የከተማዋ ህዝብ በተለያየ መንገድ ዝንባሌና
ፍላጎቱን ይገልፅልኛል በሚለው መንገድ ተደራጅቶ እንዲንቀሳቀስ፣ በፆታ፣ በማህበር፣ በንግድና በተለያዩ ማህበራትና አደረጃጀቶች እንዲደራጅና
ፍላጎታቸውን በተደራጀ መንገድ እንዲገልፁ እንዲሁም ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታም የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲወጡ ጥረት ሲያደርግ
ቆይቷል”” ህዝቡም በቀጥታ በየደረጃው በሚገኙ ምክር
ቤቶች ተወካዮቹን እንዲመርጥና በስፋት እንዲሳተፍ ተደርጓል፡፡
በዚህም በከተማችን ብቻ 38 ሺህ ያህል
የምክር ቤት አባላት የሚገኙ ሲሆን እነዚህ ዜጎች በቀጥታ በየምክር ቤቶቻቸው እንዲወስኑ የሚያስችል ስርዓት ተዘርግቷል፡፡ ከወረዳ
እስከ ከተማ ምክር ቤቶች ማለት ነው፡፡ በአገር ደረጃም ከታየ ከአምስት ሚሊየን ህዝብ በላይ በየደረጃው በሚገኙ ምክር ቤቶች በቀጥታ
እንዲወስን አስችሎታል፡፡ ሌላው ህዝብም በየጊዜው እየተገኘ ስለ ኑሮው፣ ስለመልካም አስተዳደሩ፣ ስለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታውና
ስለሰላሙ እንዲመክር ችግሮችን እንዲያነሳና እንዲከራከር፣ መፍትሄ እንዲያስቀምጥ የሚያደርግበት ምቹ የፌዴራሊዝም ስርዓት አለው፡፡
ይህ በሀገራችን ያልነበረ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት ትልቅ ለውጥ አምጥቷል፡፡
ከልማት አኳያም የከተማችን የመሰረተ ልማት
ስራን ስንመለከት በከተማችን ከ83 በፊት የመንገድ ሽፋናችን ከሶስት በመቶ በላይ የማይበልጥ ሲሆን በመጀመሪያ የእድገትና ትራንስፎርሜሽን
እቅድ ስንጀምርም ከዘጠኝ በመቶ በላይ አላለፈም ነበር፡፡ አሁን ላይ ግን እስከ 21 በመቶ የደረሰበትና የመንገድም ጥራት ደረጃውን
የጠበቀ ዘመናዊ መንገድ መስራትና መገልገል ችለናል፡፡
ከተማችን በኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው
ከ83 ዓ.ም በፊት በጣም የተጎሳቆለች ከተማ የነበረች ስትሆን በአሁኑ ሰዓት ግን በሁለት መንገድ ዘመናዊ ከተማ እየሆነች ትገኛለች፡፡
በሁለት መንገድ ስንል በመንግስት ቤቶች ልማት ፕሮግራም ደሀና መካከለኛ ገቢ ያለውን ነዋሪ ተጠቃሚ የሚያደርግ የቤት ልማት እየተከናወነ
ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ባለሀብቱ የተለያዩ ሪልስቴቶች የራሱን መኖሪያ ጭምርና የተለያዩ የመገልገያ ህንፃዎችን በመገንባት ከተማዋ
ከተጎሳቆለና ለማየት ከሚያስጠላ መንደርነት ወጥታ በዘመናዊ ህንፃዎችና መንደሮች እየተለወጠች ትገኛለች፡፡
በቤት ልማት ኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ
በአሁኑ ሰዓት የቤት ችግርን ከመቅረፍ ባሻገር ለበርካታ ዜጎች የስራ እድል መፍጠሪያና በኢንዱስትሪው መስክ በርካታ ኢንዱስትሪያሊስቶች
እየፈሩበት ነው፡፡ ወጣቱ በጥቃቅንና አነስተኛ ተደራጅቶ በመስራት ተጠቃሚነቱን እያረጋገጠ ጥሪት በመቋጠርና ወደ ባለሀብትነት እየተሸጋገረ
ነው፡፡ ሌላው የተቀናጀ የመኖሪያ አካባቢም ከመፍጠር አንፃር ዘመናዊ መንገድ፣ ፍሳሽ ማስወገጃ፣ ትምህርት ቤቶች፣ የህክምና ተቋማት፣
አረንጓዴ ልማትና በርካታ የአገልግሎት መስጫ ተቋማት ከአፈፃፀም አንፃር ክፍተት ቢኖርባቸውም በተሳካ ሁኔታ የተቀናጀ የመኖሪያ ሁኔታ
መፍጠር ተችላል፡፡
19 HÄs¤
የካቲግንቦት 20 qN 2008
በሌላ በኩል ይህ የቤት ግንባታ የመኖሪያ ቤት እጦት ችግር ከመቅረፍ በዘለለም ፍትሃዊ የሀብት ክፍፍልን ያረጋገጠ
ሆኗል”” በዚህም በቤቶች ልማት ፕሮግራማችን ከ600
ሺህ ህዝብ በላይ ተጠቃሚ የሆነበትን ስርዓት ፈጥረናል፡፡ አሁንም በስፋት እየተገነባ ነው፡፡ በአሁኑ ሰዓት እየተሰሩ ያሉ መሰረት
ልማቶች እየተለመዱ በመምጣታቸውና ልማቱም እንድሚቀጥል ህዝቡ በመተማመኑ ከዚህ ቀደም ስንሰራና ስንጨርስ ብርቅ ይሆኑብን የነበሩ
ልማቶች አሁን ላይ ትላልቅ ሜጋ ፕሮጀክትም ስንሰራ ምንም የማይመስለው ትውልድ እየበዛ መጥቷል፡፡ ይህ ማለት እየለመደው ስለመጣ
ማለት ነው፡፡ ሆስፒታሎቻችንን ብናይ ከዚህ በፊት አንድ ህንፃ ገንብተን ካጠናቀቅን በጣም ብዙ ይወራለት የነበረ ሲሆን አሁን ላይ
በአምስቱም ሆስፒታሎቻችን አምስት ዘመናዊ ትላልቅ ህንፃዎችን እንደ አዲስ ሆስፒታል ገንብተን አጠናቀን ወደ ስራ አስገብተናል ነገር
ግን እንደ አዲስ የማይታይበት ሁኔታ ነው ያለው ለምን ሲባል ልማት በህዝቡ ዘንድ መደበኛ ስራ መሆኑን አረጋግጧልናል፡፡
በትምህርት መስክ ከመጀመሪያ ደረጃ እስከ ሁለተኛና ከፍተኛ ተቋም ድረስ ህንፃ ገንብቶ ወደ ስራ ማስገባት እንደ
መደበኛ ስራ ነው እየታየ የመጣው፡፡ በባቡር ትራንስፖርትም ብዙ ሰው በእድሜአችን እናየዋለን ብሎ የማይገምተው ነገር በተግባር በአጭር
ጊዜ ተጠቃሚ የሆነበት ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡ የከተማዋን የትራንስፖርት ችግርም ለመቅረፍ በጣም በርካታ የማሻሻያ እርምጃዎች እየተወሰዱ
ነው፡፡
ከመልካም
አስተዳደርና ከአገልግሎት አሰጣጥ
አንፃር በርካታ
ችግሮች አሉ፡፡
ነገር ግን
ለማሻሻል ሪፎርም ተዘጋጀቶ
ተግባራዊ ለማድረግ ጥረት
እየተደረገ ነው፡፡ ባጠቃላይ
ሲታይ የዴሞክራሲ
ስርዓት ግንባታችንን
ለማሻሻል ህዝቡንም የልማቱ
ተሳታፊና ተጠቃሚ ለማድረግ
እየተደረገ ያለ ጥረትና
ውጤቱ በሁሉም
መስክ የሚጨበጥና
የሚታይ ለውጥ
እየመጣ ነው፡፡
በዚህም የከተማችን
ህዝብ የተረጋጋ
ህይወት እንዲመራ
የሚያስችል ውጤት ነው
እየተመዘገበ ያለው፡፡ ይሄ
ደግሞ የግንቦት
20 ፍሬና ቱሩፋት ነው፡፡
ህዳሴ፡-
የአዲስ አበባ
እድገት በሀገራችን
የከተሜነት አስተሳሰብና እድገት
እንዲመጣ ምን አስተዋፅኦ
እያደረገ ነው?
አቶ ተወልደ፡- ከተማችን
አዲስ አበባ
ዋና የሀገሪቷ
ማዕከል አንደመሆኗ
መጠን ለሌሎች
ከተሞች ምሳሌ
መሆን አለባት፡፡
ይጠበቅባታልም፡፡ እስካሁንም ለሌሎች
ሞዴል የሆኑ
ስራዎችን እየሰራች ነው፡፡
ልምድ የሚፈልግ
አካል እንደ
አወሳሰዱ ነው”” በእኛ ከተማ እየተሰራ ያለው ሁሉም ስራ ግን ለልምድ ተብሎ
ሳይሆን ለከተማው እድገትና ለህዝቡ ተጠቃሚነት በማሰብ ነው”” እግረ
መንገዱን ግን የሚሰራው ስራ ለሌሎች ከተሞች ብቻም ሳይሆን ለሌሎች ሀገሮችም ልምድ የሚወስዱበት ቢሆን ችግር የለውም፡፡ እስካሁንም
የሀገራችንን የክልል ከተሞች እንተውና በአፍሪካ ደረጃ እንደኛ በቤቶች ልማት እየተሰራ ያለውን ግዙፍ የቤቶች ፕሮግራም መስራት አልቻሉም፡፡
ብዙ የአፍሪካ ሀገሮች አሁን ላይ ከቤቶች ልማት ፕሮግራማችን ልምድ እየወሰዱ ነው፡፡ ከመንገድም ልማት ፕሮግራማችንም እንዲሁ፡፡
በአጭር ጊዜ ይህን ያህል መጠነ ሰፊ የመንገድ ልማት የሚያካሂድ ሀገር ከሰሃራ በታች የለም፡፡
ስለዚህ
ለሀገራችን ከተሞች ብቻም ሳይሆን ለአፍሪካ ሀገራት ልምድ ሊሆን የሚችል ውጤት ነው እየተመዘገበ ያለው፡፡ በተለይ ህዝብን በማሳተፍ
የአካባቢ ልማትን የማረጋገጥ ጉዳይም በምሳሌነት ሊወሰዱ የሚችሉ በርካታ ነገሮች ከተማችን ላይ እየተሰሩ ነው፡፡ ዋናው ነገር እኛም
ከሌሎች እንማራለን ሌሎችም ከኛ ከተማ ስራዎችና ልማቶች ይማራሉ፡፡
ህዳሴ፡-
ይህ ሁሉ ውጤታማ ስራ ከተሰራ እንደ ተግዳሮት የሚነሱ ነገሮች ምን ምን ናቸው?
አቶ
ተወልደ፡- የህዳሴአችን ጉዞ የሚያጓትትና የሚያደናቅፍ ምናልባትም በከፍተኛ ቁርጠኝነትና ትግል ካልተቀረፈ ወይም ካልተፈታ ሊያደናቅፉን
የሚችሉ ማነቆዎች አሉ፡፡ አንዱ ፖለቲካው ኢኮኖሚው ነው፡፡ ፖለቲካ ኢኮኖሚው ለኪራይ ሰብሳቢነት የሚያመች ስለሆነ ነው፡፡ አጠቃላይ
ስርዓቱ በእድገትና ታዳጊ ስለሆነ ብዙ አሰራሮቻችን ኋላ ቀር ናቸው፡፡ አመለካከታችን ኋላ ቀር ነው፡፡ ነገር ግን በየጊዜው እድገት
ቢኖርም አሁንም ከኋላ ቀርነት አመለካከትና ተግባር የተላቀቅን አይደለንም፡፡ ስለዚህ ኪራይ ሰብሳቢነት ስንል መገለጫው ብዙ ነው፡፡
በአንድ በኩል ባልሰራህበት ለስራህ ለድካምህ የማይመጥን የስራህ የድካምህ ዋጋ ያልሆነ በአቋራጭ የመክበርና የመለወጥ ተግባር ዘረፋ
ስርቆት ይሄ አንዱ መገለጫ ነው፡፡ ከመነሻችንም ነበረ አሁንም አለ፡፡ ትልቁ ማነቋችንም ይሄ ነው፡፡ ይህ ደግሞ በመንግስትና በህብረተሰቡ
ውስጥ ያሉ ኪራይ ሰብሳቢዎች ተሳስረው የሚፈፅሙት ስለሚሆን ችግሩ በሁሉም ዘንድ ነው ያለው፡፡ እንደ ግለሰብ ሳይሆን እንደ ህብረተሰብ
ነው ልንታገለው የሚገባው፡፡ ስለዚህ ከስርአቱ ትልቁ ማነቆ አንዱና ዋነኛው ኪራይ ሰብሳቢነት በመሆኑ በትጋት ልንታገለውና ከምንጩ
ልናደርቀው ይገባል፡፡
ሁለተኛው ማነቆ ኋላ ቀር አመለካከቶች የትምክህት፣ የጥበት፣
የአክራሪነት አመለካከቶች አሉ፡፡ ሙሰኛው ሌላ በነዚህ ውስጥ ነው የሚደበቀው፡፡ እነዚህን በመጠቀም ነው የራሱን ትርፍ የሚያግበሰብሰው፡፡
ትምክህት፣ ጥበት፣ አክራሪነት ሲባል ተራ ቃላት ሊመስሉ ይችላሉ ነገር ግን ሀገር የሚያጠፉ ናቸው፡፡
በትምክህትና በጥበት የሚገለፁ በተለያዩ አካባቢዎችም የሚታዩ
ምልክቶች አሉ፡፡ በአክራሪነትም በተመሳሳይ መንገድ””
በሀይማኖት ሽፋን ፍላጎትን በሌላው እምነት ላይ ለመጫን የሚደረጉ
እንቅስቃሴዎች በሙሉ ሀገር የሚያጠፉ ናቸው፡፡ በነዚህ ጥላስር ደግሞ ሌላ ሊሸጉጥ ስለሚችል እንደተራ ጥበት፣ ትምክህት፣ አክራሪነት
ተብሎ ሊወሰድ አይገባም፡፡ በጣም ትልቅ የስርዓታችን ጋሬጣና እንቅፋቶች ናቸው፡፡ ስለዚህ ዋናው የህዳሴ ጉዟችን ዋነኛ ማነቆ ኪራይ
ሰብሳቢነት ነው፡፡ ስለዚህ ህዳሴአችንን በተጠናከረ መንገደ እንዲቀጥል ከሆነ በላቡና በጥረቱ ውጤት ለመጠቀም የሚያስብ ዜጋ መፍጠር
አለብን፡፡
ይህንን ዜጋ ከፈጠርን አመራራችን የዜጋው ተምሳሌት ነው ይሆናል
እንደ ህብረተሰብ እንደዚህ አይነት አስተሳሰብ ካልተፈጠረ ግን አመራሩም ከህብረተሰቡ ነው የሚፈጠር፡፡ ስለዚህ አመራሩ ይህን ኋላ
ቀር አመለካከትና ተግባር ሰብረህ ውጣ ነው እንጂ እየተባለ ያለው እርሱ አይደለም የፈጠረው፡፡ ችግሩን የፈጠረው አጠቃላይ ፖለቲካል
ኢኮኖሚው ነው፡፡ ነገር ግን ፖለቲካል ኢኮኖሚውን የመቀየር ሀላፊነት ተሰጥቶታል ለአመራሩ፡፡ የተሰጠውን ሀላፊነት ግን በአግባቡ
እየተወጣ አይደለም፡፡ ይጎትተዋል፡፡ ፖለቲካል ኢኮኖሚው እየጎተተ ወደ ጭቃው ያዘቅጠዋል ማለት ነው፡፡ ስለዚህ አሁን ዋናው ችግራችንን
ማነቋችን ከኪራይ ሰብሳቢነት ፖለቲካል ኢኮኖሚ የሚነሳ የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባር ነው፡፡ ይሄም በመኖሩ ለልማታችን፣
ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታችን እንቅፋት እየሆነ ነው፡፡ ይህን መፍታት አለብን፡፡
ልማታዊው ሀይል እንዲጎለብት ኪራይ ሰብሳቢነትም እንዲቀጭጭ
ማድረግ አለብን በአሰራር በአደረጃጀት በአመለካከት ግንባታ በሁሉም መጠነ ሰፊ እንቅስቃሴ ካልተደረገ የኪራይ ሰብሳቢነት አደጋ ትልቅ
ፈተና ነው፡፡ የስርዓታችንና የህዳሴ ጉዟችንም ትልቅ ፈተናና አደጋ ነው ተብሎ ሊወስድ ይችላል”” መፍትሄውም ህብረተሰባዊ ለውጥ ማምጣት ነው፡፡ የኪራይ ሰብሳቢነት ፖለቲካል ኢኮኖሚውን ለመቀየር
አንደኛና ዋነኛው መፈትሄ እድገቱን ማፋጠን ነው፡፡
ህዳሴ፡- እናም እድገቱ ራሱ ፖለቲካል ኢኮኖሚውን እየቀየረ
ይሄዳል እያልን ነው?
አቶ ተወልደ፡- አዎ! እድገቱ ራሱ ፖለቲካል ኢኮኖሚውን እየቀየረው
ይሄዳል፡፡ ስለዚህ እድገቱን በትክክል አቅጣጫ ማስኬድ ይጠይቃል፡፡ ህዝቡንና ዜጋውን ተጠቃሚ እያደረገ ከሄደ፣ እድገቱ ደግሞ መዋቅራዊ
ሽግግር ካረጋገጠ ከአገልግሎት ወደ ማኒፋክቸሪንግ ቋሚ ወደሆኑ መዋቅሮች እየተሻገገረ የሚሄድ ልማት ከሆነ ልማታዊው ፖለቲካል ኢኮኖሚው
ኪራይ ሰብሳቢ ፖለቲካል ኢኮኖሚውን አሽመድምዶ ይጥለዋል፡፡ መዋቅራዊ ሽግግር ስንል በሁለት መንገድ ነው፡፡ አንደኛ በኢኮኖሚ መዋቅራዊ
ሽግግር መምጣት አለበት፡፡ ወደ አምራችነት በተለይ የኢንዱስትሪ አምራችነት የሚያሸጋግር ሁለተኛ የአመለካከት ለውጥ ማምጣት አለብን፡፡
ይህንን የሚያፋጥን የውስጠ ድርጅት ጥራትና ጥንካሬ ትግል ማጠናከር አለብን፡፡ በህብረተሰቡ ውስጥ ደግሞ ትግል የመለኮስ ስራ መስራት
ድርጅቱንና መንግስትን መልሶ እንዲያጠናክር ሰፊ የህብረተሰብ ተሳትፎ እንዲኖር ማድረግ ይኖረብናል፡፡ ልማታዊ ሰራዊት ብለን እንዳስቀመጥነው
የድርጅት የመንግስትና የህዝብ የተቀናጀ እንቅስቃሴ ነው የአመለካከት ለውጥ የሚያመጣው፡፡ ተግባራዊ ማድረግ ነው ያለብን፡፡
ህዳሴ፡- ለመላው የከተማችን ህዝብ ግንቦት 20ን አስመልክተው
የሚያስተላልፉት መልዕክት ካለ?
አቶ ተወልደ፡- በመጀመሪያ እንኳን ለ25ኛው አመት የግንቦት
20 የድል በዓል በድጋሚ በሰላም አደረሳችሁ እላለሁ፡፡ በመቀጠልም አሁን ላይ ሆነን የግንቦት 20 የድል በዓል ስናከብር የምናያቸውና
በውል ልናስተውላቸው የሚገቡ ነገሮች አሉ፡፡ አንደኛው በጣም ተስፋ የሚሰጡ ለውጦችን ያስመዘገብንበት በፈጣን የእድገት ጎደና የምንራመድበት
እድገት ማምጣትና ልንለወጥ የምንችል ህዝቦች መሆናችንን ያረጋገጥንበት ጉዞ ነው የተጓዝነው፡፡
በተለይ ከተሃድሶ በኋላ ለ14 ዓመታት ያሀል ባለመቋረጥ በአማካይ
ባለድርብ አሀዝ እድገት በተከታታይ አስመዝግበናል፡፡ ይሄ ደግሞ በብዙ ሀገሮች ያልታየና እኛ ግን ተግባራዊ ያደረግነው የእድገት
ጉዞ ነው፡፡ ይሄ የሚያሳየን ነገር ምን ያህል የተሀድሶ መስመርና የተሀድሶ ፖሊሲና ስትራቴጂዎቻችን የለውጥ ፖሊሲና ስትራቴጂ መሆኑን
ያሳያል፡፡ ያስመዘገብነው ለውጥ መሰረተ ሰፊ ሁሉም ብሄር ብሄረሰቦች እኩል የተጎናፀፉት ነው፡፡ ይሄ ደግሞ የግንቦት 20 ቱሩፋትና
ፍሬ ነው፡፡ ይህ በያዝነው መንገድ ከቀጠለ ለውጡ በጣም አስተማማኝና በአጭር ጊዜም መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት ተርታ እንድንሰለፍ
የሚያስችል ሁኔታን የሚያረጋግጥ ነው፡፡
የሩብ ክፍለ ዘመን ሂደታችንን ስንገመግም፡፡ በአንድ በኩል
አሁን እየተፈጠረ ያለና ሂደቱ የሚፈጥራቸው በሌላ በኩል ሂደቱ የሚፈጥራቸውና እየታዩ ያሉ ዝንባሌዎች ይህንን ፈጣን የህዳሴ ጉዟችንን
አዳጋ ላይ ሊጥሉ የሚችሉ ነገሮች ግን አሉ፡፡ ጠያቂ ህብረተሰብ ተፈጥራል፡፡ ይህ ጠያቂ ህብረተሰብ የተፈጠረው ደግሞ በተሀድሶ መስመራችን
ነው፡፡ ጠያቂ ህብረተሰብ ከሌለ ደግሞ ለውጥ የለም ለውጥ የሚፈልግ ህብረተሰብ መፍጠር ነው ያለበን ብለን ነው የፈጠርነው፡፡ ድርጅታችንና
መስመሩ የፈጠረው ነው፡፡ ነገር ግን ራሱ ህብረተሰቡን ለማሳተፍ ከፖሊሲያችን ስትራቴጂዎቿችን የመነጩ አሰራሮችና መርሆዎችን መሰረት
አድርገን በፍጥነት ካልመለስን ግን አደጋ ላይ እንወድቃለን ማለት ነው፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ ይህንን እንዳናደርግ የሚያደርገን
የኪራይ ሰብሳቢነት አመለካከትና ተግባርን በቁርጠኝነት ለመታገል አመራሩና አባሉ ህዝቡ በተደራጀ መንገድ ለመብቱ ሲታገል ነው”” ህዝቡ መብቱን በገንዘብ መሸጥ የለበትም፡፡ መብቱን በገንዘብም መግዛት የለበትም፡፡ አመራሩ
መንግስትና ህዝብ የሰጠውን ተልዕኮ በአግበቡ መወጣት አለበት፡፡ ህዝቡ መብቱን በትግል ማስተካከል ሲችል ደግሞ የኪራይ ሰብሳቢነት
አመላከከትና ተግባር እየተናደ ልማታዊ አስተሳሰብና ተግባር እየጎለበት ይሄዳል፡፡ በዛውም ልክ የህዝቡ ተጠቃሚነት እየተረጋገጠ ይመጣል፡፡
ለውጡም የማያቋርጥና መጠነ ሰፊ ሆኖ ይቀጥላል ማለት ነው፡፡
ስለዚህ ይህንን ለማድረግ መላው አመራራችን፣ አባላችን ምልዓተ ህዝቡ መንግስትና ድርጅታችን የመልካም አስትዳደርን ችግር ለመፍታት፣
ኪራይ ሰብሳቢነትን ከስር መሰረቱ ለመናድ እና ልማታዊ አስተሳሰብንና ልማትን ለማፋጠን ቆርጦ እንደተነሳ ሁሉ ከድርጅታችንና ከመንግስታችን
ጎን ተሰልፎ ባለፉት አመታት ያስመዘገባቸውን ድሎች ወደፊትም በማስቀጠል የህዳሴ ጉዟችንን ለማፋጠን በሩብ ክፍለ ዘመኑ የድል በዓል
ቃል ኪዳን ገብተን አብረን ልንታገል ይገባል የሚል መልዕክት አስተላልፋለሁ፡፡