Friday, 25 September 2015

የወጣቶች የትግል ጉዞና የቀጣይ ዘመን ተልዕኮ(ለፍትህና እኩልነት የተከፈለ ዋጋ)

ለፍትህና እኩልነት የተከፈለ ዋጋ
የኢትዮጵያ ብሄሮች፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች በወቅቱ በነበሩት ዴሞክራሲያዊ ድርጅቶች ህወሓትና ኢህዴን/ብአዴን ኋላም ኦህዴድ ውስጥ በመታቀፍ ወጣቱ ሲያነሳቸው ከነበሩት ጥያቄዎች የህዝባዊ መንግስት ምስረታ፣ የእኩል ተጠቃሚነት፣ የብሄርና የኃይማኖት እኩልነት፣ የፍትህና ዴሞክራሲ ጥያቄዎችን ለመመለስ በኢህአዴግ ጥላ ስር ሆነው በፅናት የትጥቅ ትግል አካሂደዋል። በርካታ መስዋዕትነትም ከፍለዋል። ብረት አንስተው በትጥቅ ትግሉ ፍልሚያ የተሳተፉ ታጋዮች ብቻም ሳይሆኑ ንፁሃን የአገራችን ጭቁን ህዝቦች በደርግ የጦር አውሮፕላኖች ዘግናኝ በሆነ መልኩ በጋራ የተፈጁባቸው እንደ ሀውዜን፣ መርሳና በለሳ ያሉ መንደሮች ለፍትህ፣ ለዴሞክራሲና ለብሄር እኩልነት መረጋገጥ ሲባል የተከፈሉ መራር መስዋዕትነቶችን አጉልተው አሳይተዋል። በደርግ የአፈና መዋቅር ከመማረክ ራስን ማጥፋትን የመረጡ ወጣት ታጋዮች በደርጎች እጅ ወድቀው እንኳ ከቆሙለት ዓላማ ፍንክች እንዳላሉ አረጋግጠዋል። እንደ ህወሓት ጓዶች አሞራው (ወልደገሪማ)፣ ቐሺ ገብሩ (ሙሉ ገብረእግዚያብሄር) እንዲሁም እንደ ኢህዴን/ ብአዴን ጓድ ዘለቀ ደምሴ ያሉ በደርግ የግፍ በትር የተገደሉ ታጋይ የኢትዮጵያ ወጣቶች የኢህአዴግ የዓላማ ፅናትና ለህዝቦች ጥቅም ሲባል የተከፈለ መስዋዕትነት የሁልጊዜም ማነፃፀሪያዎች ናቸው። ደርግ ሲያደርሰው ከነበረው ጭፍጨፋ ባሻገር የአገሪቱን ኢኮኖሚ በማዳከም ህዝቡን ለከፋ ድህነት ዳርጓል።

የወጣቶች የትግል ጉዞና የቀጣይ ዘመን ተልዕኮ


በፊውዳሎችና አምባገነኖች ጭቆና ለዘመናት ፍዳቸውን ሲያዩ ከቆዩት የአገራችን ህዝቦች ዋነኛው ገፈት ቀማሽ አርሶ አደሩ ነበር። የከተማ ወጣቶችና ሴቶች የፍትህና የዴሞክራሲ ጥያቄዎችን በማንሳት ለለውጥ ከመሰለፍ ባሻገር አርሶ አደሩ በመሬቱና በምርቱ እኩል ተጠቃሚ ይሁን ብለው በመጠየቃቸው የጭፍጨፋ ሰለባ መሆናቸውም አይዘነጋም፡፡ እነዚህን ጥያቄዎች በማንሳት በተለያዩ ጊዜያት በተደራጀና ባልተደራጀ መልኩ የተካሄዱ ትግሎችም በአርሶ አደሩና አርሶ አደሩን ማዕከል አድርጎ በወጣቶች መሪነት የተካሄዱ ናቸው። ባልተደራጀ መልኩ ጭቆናን ለመናድ በተደረጉ ሙከራዎች የቀዳማይ ወያኔ ትግልና የጎጃምና የባሌ አርሶ አደሮች ያካሄዷቸው አመፆች በቀዳሚነታቸው ይጠቀሳሉ። ምንም እንኳ እነዚህ ያልተደራጁ እንቅስቃሴዎች በወቅቱ ባይሳኩም የወቅቱ ወጣቶች ካለፈው በመማር ጠንካራ የትግል አደረጃጀት እንዲከተሉ መሰረት ሆነዋል፡፡

Wednesday, 16 September 2015

Ethiopia poised to be fastest-growing country in the world: Gates Report



The Gates Foundation has released a report “One foot on the ground, one foot in the air” tracking ‪#‎Ethiopia‬’s development which highlighted major strides in massive agricultural investment, a sector which employs three in four Ethiopians and a government committed to pro-poor spending to halve its poverty. According to the report, the agricultural sector has cut poverty by seven per cent between 2005 and 2011. With Ethiopia’s development finding its roots in an agriculturally-led environment, it has included, “Maintaining teams of agronomists across vast rural areas to boost productivity by recommending best agricultural practices and scientific innovation. "Further, a doubling of Ethiopia’s road network in two decades, which has allowed more farmers to bring their produce to market," said the report.
The notable takeaway lessons from Ethiopia’s experience in sustainable developmental goals is firstly, “Centering government policy on a single goal - poverty reduction - and taking a multidimensional approach can encourage ministries to work more comprehensively and consistently.”Another strategy is, “Integrating social sectors into broader economic planning and high rates of pro-poor spending benefit the economy.” Thirdly, “Long-term planning and a clear division of responsibilities can build the foundation for broader transformation.”
Another key driver of poverty reduction is Ethiopia’s Productive Safety Net Programme (PSNP), Africa’s largest social protection scheme, which pays seven million Ethiopians in food or cash in exchange for work on agricultural-infrastructure projects that maintain food security and reduce the incidence of famine.
“The PSNP mobilises 10 per cent of the population (1.5 million households) to stabilise food supply cutting poverty nationally by 7 per cent since 2005.”Further key findings have now predicted Ethiopia to be the fastest-growing country in the world over the next three years. But unlike other nations, most notably China, Ethiopia has achieved this growth while maintaining its low level of inequality. Ethiopia’s human resource development plan centres on education, which alongside the building of physical infrastructure, is seen as a path to structurally transform the economy and to create more jobs. Ethiopia has nearly universalized primary education, flipping primary enrollment from under one in five in school to under one in five out of school. But “One foot on the ground, one foot in the air” also highlights the challenges that remain. Improvements in access to education (e.g. 190% increases in number of primary schools between 1997 and 2012/13) has often not been met by similar improvements in the quality of education. Despite gains in agricultural productivity and declines in rural unemployment wages remain low leaving many groups, particularly in rural areas, vulnerable.

መልካም አስተዳደር የአዲሱ ዓመት ገጸ በረከት (1) ዮናስ


በማደግ ላይ ባለችው ኢንቨስት ማድረግ (Investing in emerging Ethiopia) ለተባለ እና ለ3ኛው ዓለም አቀፍ
የፋይናንስ ጉባኤ የተሠናዳ መጽሄት ጠቅላይ ሚንስትር ሃይለማርም ደሳለኝ እንዲህ አሉ፡፡ “ላለፉት 12 ዓመታት የኢትዮጵያ
ኢኮኖሚ ተከታታይ የሆነ የ11 በመቶ እድገት አሳይቷል፡፡ ይህ እድገት ደግሞ ከዘይትና ተፈጥሮ ሀብት የነፃና በዓለም አቀፍ
ደረጃ በፍጥነት እያደጉ ከሚገኙ 10 ሀገራት መካከል አንዷ እንድትሆን ያስቻለ ነው፡፡
ጠቅላይ ሚንስትሩ ያሉትን በተመሳሳይም አለም አቀፍ የምጣኔ ሃብት ተመራማሪዎችና የገንዘብ ተቋማት ያረጋገጡና የመሰከሩ
ሲሆን ፤ጠቅላይ ሚንስትሩም አያይዘው ሲገልጹ ለዚህ ለእድገት መንግስትና የግሉ ዘርፍ ዋና ሞተር ሆነው ስለመስራታቸውና
ለዚህም የመንግስት ድጋፍና ማበረታቻዎች እጅግ የላቁ እንደነበር በማውሳት ነው፡፡
We recognize that the private Seter should be the engine of our growing economy. The
government is thus committed to provide support and ensure a conductive policy and
regulatory environment for private investment
2ኛውን ዙር የእድገትና ትራንፎርሜሽን ተግባራዊ አፈጻፀም ለመጀመር ከዋዜማው ላይ የሚገኘው መንግስታቸውን
በተመለከተ ጠቅላይ ሚንስትሩ ሲናገሩ፣ መንግስታቸው ለግሉ ሴክተር የሃገር ውስጥም ሆነ የውጭ ኢንቨስትመንት በሰው
ሃብት ልማትና ኃይል እንዲሁም የመሰረተ ልማት ዘርፍ ምቹ የፖሊሲ ማኑዋል ስለማዘጋጀቱ እና በዚህም ለበለጠ እድገት
መብቃት የሚችልባቸውን ሁኔታዎች ማመቻቸቱን ነው፡፡
My governments commitment for the expansion of private investment our Massivee
investments in human resorce development energy and infrastructure and our policy frame
works are providing to be effective in expanding domestic investment and attracting forign
direct investment.
ለዚሁ መጽሄት ተመሳሳይ ስለሆነው ጉዳይ ተመሳሳይ ምላሽ የሠጡት የፋይናንስ እና ኢኮኖሚ ልማት ሚንስትር ዴኤታ
ዶ/ር አብርሃም ተከስተ፣ ኢትዮጵያ አሁንም ትኩረት አደርጋ በመስራት ላይ ያለችው ለኢንዱሰትሪው ዘርፍ መዋቅራዊ
ለውጥ ማምጣት በሚያስችል ፈጣን አግባብ ነው፡፡ በተለየ እና ለውጡም በሥራ ፈጠራና የወጪ ንግድን መሰረት ያደረገ
ነው፡፡
Ethiopia is making concerted efforts to acclerate the process of industrialization and
structural transformation bay focusing in particular on job creating and export oriented
manufacturing industries
2
ይህንኑ መጽሄት ከሌሎች ዓለም አቀፍ የምጣኔ ሃብት ተቋማት ጋር በመሆን ያሳተመው ድርጅት ማኔጂንግ ፓርትነር አቶ ዘመዴነህ ንጋቱ፣ ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ ኢንቨስትመንት ምቹ የሆነችበትን ይልቁንም በአሜሪካ፣ አውሮፓና ኤዢያ ኩባንያዎች የሚለውን ጥያቄ በሚገባ የፈተሸ ሪፖርት እንደሆነም አውስተዋል፡፡
እናም ለዚህ ጥያቄ ምላሽ ሠጥቷል የተባለው መጽሄት የዓለም ባንክን መረጃ መሠረት በማድረግ ስለ ኢትዮጵያ መመቸት በተለይም ለምእራባውያኑ ቀልብ መሳብ ምክንያት ናቸው ሲል 10 ጉዳዮችን ያነሳል፡፡ ከእነዚህና ኢትዮጵያን በፍጥነት በማደግ ላይ ከሚገኙ 10 ሀገራት መካከል ይልቁንም ከአፍሪካ በ82 በመቶ በሦስተኛ ደረጃ ላይ እንድትገኝ ካስቻሏት ነጥቦች መካከል አንዱና በ9ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠው የሚያሠራ ክበብ( operating environment) ነው የተባለው የዚህ ጽሑፍ አጀንዳ ነው፡፡
ከላይ በተመለከቱትና መጽሄቱም በዝርዝር እንዳሰፈራቸው እንደ ኢትዮጵያ የመመቸት ነጥቦች ቢሆን ኖሮ ከበላይዋ ከተቀመጡ 2 የአፍሪካ ሃገራት ፤ደቡብ አፍሪካ እና ጋና ቀዳሚ በነበረች የሚያስበሉ በርካታ ጉዳዮች ቢኖሩም ፤ ከነዚህ ጉዳዮች ውስጥ አንዱና ለሁለተኛው ዙር እቅድ ዘመን መጀመሪያ ዓመት ለሚሆነው አዲስ አመታችን ከመንግስት የምንጠብቀው ገጸ በረከት መልካም አስተዳደር ነው፡፡
የመልካም አስተዳር ጉዳይ ለሁለተኛው ዙር እቅድ ዘመን የህልውና ጉዳይ በመሆኑ መሪ ድርጅቱ በጉባዔው ያሰመረበትም ዋንኛ ምክንያት ይህና ከመልካም አስተዳደር ጋር የተያያዘው ችግር እንደ ልብ አላላውስ በማለቱ ነው፡፡ አሁንም ኢትዮጵያ ከአንደኛው ዙር በቀመረችው ተሞክሮም ሆነ ለዚሁ ሲባል በቀረጸችው ተያያዝ ለመትጋት የተዘጋጀች መሆኑ ቢታወቅም፡፡ ስለዚሁ በተዘጋጁ መድረኮች ከተገኙ በርካታ ግብአቶች መካከል የዚህ ጽሁፍ ትኩረት የሆነው አላላውስ ያለ መልካም አስተዳደራዊ ጉዳይ ነው፡፡
ይህ ደግሞ ልክና ሃቅ ነው፡፡ ጠቅላይ ሚንስትሩም ሆኑ ሚንስትር ዴኤታው እና ተመራማሪዎችን ጨምሮ የአለም ባንክም ባስቀመጠው ጥናት ይህች አገር ተስፋ ያላትና የአለምን ቀልብ የገዛች ነች፡፡ ይህ ቀልብ ገዢነቷ እና እድገቷ የበለጠ አስተማማኝ የሚሆነው ደግሞ ለሃገር ውስጡም ሆነ ለአለም አቀፉ የውጭ ኢንቨስትመንት የተመቸ እና የሚመጥን አገልግሎት መስጠት ስትችልና የግል ሴክተሩን የሚያበረታታ ከኪራይ ሠብሳቢነት የፀዳ ሥርአት በማያወላዳ መልኩ መዘርጋት ስትችል ብቻ ነው፡፡ ስለሆነም መልካም አስተዳደር ለአዲሱ ዓመት ከመንግስት የምንሻው ገጸ በረከት ነው ስንል እውነት ስላለን ነው፡፡
ይህ እውነት የዚህ ጹሁፍ አቅራቢ ብቻ ሳይሆን ከላይ በተመለከተው አግባብ የህዝቡ፣ የመንግስት፤ የመሪ ድርጅቱ ኢህአዴግና የልማታዊ ባለሃብቱም ነው፡፡ ስለሆነም አለም የመሰከራቸው ምቹ የኢንቨስትመንት ሁኔታዎችን ለጊዜው ተወት አድርገን ይህ እድገት እንዳይጨናገፍብን የምንሻ ከሆነ አስጊ የሆነውን የመልካም አስተዳደር ዘርፍ በደንብ ማሄሥና የመሻታችንን ተገቢነት ማጠየቅ አስፈላጊነቱ አያጠራጥርም፡፡ ስለሆነም ኢህአዴግም “ራስ ምታቴ ነው” የሚለውን የመልካም አስተዳደር ጉዳይ ከህዝቡ ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ከባለሃብቱና ከመንግስት ይልቁንም ከራሱ ከመሪ ድርጅቱ አንጻር ዘርዘር አድርገን እንዲህ እናያለን ፡፡
3
ይህ ማየታችን ደግሞ የመሪ ድርጅቱ የጉባኤ መሪ ቃልም ሆነ የሁለተኛው ዙር የእቅድ ዘመን መጀመርን ማብሰሪያው ህዝባዊ አደራን በላቀ እድገትና ትራንስፎርሜሽን የሚል ነውና የቀረን አደራም መልካም አስተዳደር ከመሆኑ የሚመነጭ መሆኑንም በመሰረታዊነት ታጤኑልን ዘንዳየጸሃፊው መሻት ነው፡፡
ይህ ማለት ግን ላለፉት 12 ዓመታት የተገኘውና ደብል የሆነው እድገት በባዶ ነው የመጣው ማለትም እንዳልሆነ ሊጤን ይገባዋል፡፡ አሁን ችግሩና ሥጋቱ ይህን ፍንጭ በተለይም ከመልካም አስተዳደር ጋር የተያያዘውን ጉዳይ ተቋማዊ መልክ ከማስያዝና ካለማስያዝ ጋር ያለው ነው፡፡
እንደሚታወቀው ከቀረጥ ነፃ የሆነ የንግድ መብት አሜሪካ ለአፍሪካ ሃገራት የሰጠችውን (AGGOA) የመሳሰሉ ማበረታቻዎች የተሰጣቸው የአፍሪካ ሃገራት የኢኮኖሚ ተወዳዳሪ መሆን አልቻሉም፡፡ ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ የመሰረተ ልማት አገልግሎታቸው ኋላቀር በመሆኑ፤ ገበያቸው በጣም ጠባብና ኢኮኖሚያቸውም እርስ በርሱ በበቂ ሁኔታ የማይመጋገብ በመሆኑ፤ እንዲሁም አዲስ ቴክኖሎጂ ማመንጨቱ ይቅርና በገበያ ላይ ያለውን በአገባቡ ትቅም ላይ ማዋል ባለመቻላቸው እንደሆነ የሚመሰክሩት አለም አቀፍ የምጣኔ ሃብት ተመራማሪዎችና ተቋማት ይልቁንም 3ኛው ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ጉባኤ እንዳረጋገጠው እነዚህ ሃገራት የመልካም አስተዳደር አገልግሎታቸው እጅግ ኋላቀር፣ ቀርፋፋና የዝርፊያ መነሃሪያ በመሆኑ ነው፡፡ ስለሆነም በሁለተኛው ዙር ስለምንሻቸው ውጤቶች ቀርፋፋና በብልጭታ ደረጃ የሚገኘው የመልካም አስተዳደር ጉዳያችን በተሟላ መልኩ የአዲሡ ዓመት ገጸ በረከት እንዲሆን እንሻለን፡፡
እድሜ ለገጠሩ እንበል እንጂ ኢህአዴግም እንዳመነውና መንግስትም ዋነኛ ሥራዬ ይሆናል ሲል በከተሞች አካባቢ ያለው የኪራይ ሠብሳቢነት ፖለቲካል ኢኮኖሚ ማየል ከማንወጣው አዘቅት ውስጥ በከተተን ነበር፡፡ ለምን እና እንዴት ስለምንስ በከተሞቻችን የኪራይ ሰብሳቢነት ፖለቲካል ኢኮኖሚ የበላይነትን ያዘ ፤ የበላይነትን በመያዙስ በኢኮኖሚያችን ላይ ምንና እንዴት ያሉ ተጽእኖዎችን አሳረፈ? በዚሁ ከቀጠለስ ወደፊት ምን ሊከሰት ይችል ይሆን? የሚሉትን ማየት ወደመፍትሄውና በገፀ በረከትነት ወደምንሻው ጉዳይ የሚያደርሰን ይሆናል፡፡
በአንደኛው ዙር የእድገትና ትራንፎርሜሽን እቅድ በፈለግነው ልክ ውጤት ማስመዝገብ ያልቻልነው የኢኮኖሚው ምሰሶ በሆነው የወጪ ንግድና የሥራ እድል ፈጠራን መሠረት ባደረገው ይልቁንም ካለን ጉልበት፣ መሬት እና ውሃ ሃብቶቻችን የተካከለ የማኑፋክቸሪነግ ኢንዱትሪ ዘርፎች ይልቅ ባለሃብቱ እና የመንግስት ቅጥረኞች በዘረጉት መረብ የኪራይ ሠብሳቢነት ፖለቲካል ኢኮኖሚ በከተሞች ላይ የበላይነትን በመያዙ ነው፡፡ በልማታዊ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓቱ ውስጥ የተሠገሠጉ እነዚህ ሙሰኞች ሥልጣንን የግል ጥቅም ለማካበት የተጠቀሙበት መሆኑና አሁንም ያሠፈሰፉበት አግባብ መኖሩ የመጀመሪያው መነሻና ስለመንቀርፈፋችንም ሆነ ስለሥጋታችን ማጠየቂያው ነው፡፡ ለምን ቢሉ፤ እነዚህን ያየ የተማረውም ሰው ሆነ ባለሃብቱ ሳይታገሉ ማሸነፍ ወደሚችሉበት የኪራይ ሠብሳቢነት ጎዳና መራመዳቸውን በሚገባ በከተሞቻችን አይተናል፡፡ የመንግስትም የግምገማ ውጤት ይህንኑ በሚገባ ያሳየናል ፡፡ በዚህ ጊዜ ታዲያ በለት ተዕለት እንቅስቃሴያችን እንዳየነውና የየካፌው አፍ ማሟሻ መሆኑን እንደምናውቀውም የመንግስትን መሻትና የኢኮኖሚ ስርአት ተከትሎ በገበያ ተወዳድሮ ለማሸነፍ የሚነሳን ባለሃብት መካሪ ያጣ እስከመባል ደረጃ ላይ ያደረሰን መሆኑም ነው ዋነኛው የስጋታችን ምንጭ ፡፡
መንግስት እንዳለውም ሆነ የመጀመሪያው ዙር የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ አፈጻጸም እንዳመለከተው በወጪ ንግድ ዘርፍ መወዳደር ቀርቶ ከርሳችንን በአግባቡ ለመሙላትም አላስቻለንም ፡፡ እንዳላስቻለን በማመንም የሁለተኛው ዙር እቅድ
4
ዘመን ዋነኛ ስራዬ መልካም አስተዳደር ይሆናል ሲል ቁርጥ አቋሙን የገለጸውም በአለም ገበያ ተወዳድሮ ለማሸነፍ የሚያስችለውን የቴክኖሎጂ አቅም እንዳይገነባ ባለስልጣኑና ባለሃብቱ በነፍስ ወከፍና በመመሳጠር ሳይወዳደሩ ወደሚያሸንፉበት ስራ በስፋት መሰስ እያሉ በመሆናቸው እንደሆነም ወደመፍትሄው ከመሻገራችን በፊት ማስመር ያስፈልጋል ፡፡
የመንግስት አገልግሎት የዝርፊያ መነሃሪያ በሚሆንበት ጊዜ ደግሞ ቀልጣፋና ፍትሃዊ የሆነ ተወዳዳሪነት ሊጎለብት የማይችል መሆኑ እሙን ነው፡፡ ስለሆነም ስለኢኮኖሚያችን ዘላቂነት ዋነኛው መዘውር ስለሆኑት የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትና የወጪ ንግድ ይህ ስር የሰደደ የኪራይ ሰብሳቢነት ፖለቲካል ኢኮኖሚ በከተሞቻችን መንሰራፋቱ ነው አሳሳቢ የሆነብን፡፡
በኢትዮጵያ ዴሞክራሲንና መልካም አስተዳደርን የመገንባትና የማስፈን መነሻዎች በህገመንግስቱ ላይ የሰፈሩ የዴሞክራሲ መርሆዎች በመሆናቸውም ያለአንዳች መንጠባጠብ በአዲሱ አመት እንሻቸዋለን፡፡ የዴሞክራሲ ባህልን ለመገንባት ባጠቃላይ የተማረና አቅም ያለው ዜጋ ማፍራት መሠረቱ ሆኖ የስነዜጋ ትምህርት ማስፋፋትና ጥራቱን ማረጋገጥ፣ ወጣቱ ዴሞክራሲያዊ ባህሉ እንዲያድግ የሚያግዙ ተቋማትን መፍጠር፣ በብሄረሰቦች፣ በሴቶች፣ በሃይማኖት እኩልነት ላይ የተስተካከለ አመለካከት ማሳደርን የተመለከተው አጀንዳም የአዲሱ አመት መሻታችን ነው ፡፡
ከዴሞክራሲ ባህል ግንባታው ጎን ለጎን ተቋማትም መገንባት አለባቸው፡፡ ዴሞክራሲያዊነትን የሚፈጽሙና የሚያስፈጽሙ ተቋማት፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተስተካከለና በሰከነ አቅጣጫ እንዲንቀሳቀሱ ማብቃት፤ ሚዲያንና የህዝብ ምክር ቤቶችን ሁሉ ማጠናከር ግድ የሚልበት አዲስ አመት ሊሆንም ይገባል፡፡ መልካም አስተዳደርን ከማስፈን አንፃር ቀልጣፋና ውጤታማ አገልግሎት መስጠት፣ ግልጽነትና ተጠያቂነት ማስፈን፣ ተሳትፎና የጋራ መግባባት መፍጠር፣ የህግ የበላይነትን ማስፈን፣ እኩል ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ - የተቋማትን የአገልግሎት ቅልጥፍና - ቅልጥፍና ብቻ ሳይሆን ውጤታማነት ዕውን ማድረግ ድርጅቱ በጉባኤው ያሰመራቸው ናቸውና በገጸ በረከትነት ለአዲሱ አመት እንሻቸዋለን ፡፡
ኢትዮጵያ ለዘመናት ማንነትን በሚያዋርድ የድህነትና መሃይምነት አረንቋ ውስጥ ቆይታለች፡፡ ከደርግ ውድቀት በኋላ እየተገነባ የመጣው ስርዓት አሳፋሪውን ሀገራዊ ሁኔታ ፈጽሞ ለመቀየር ባደረገው ጥረትና ርብርብ ሚሊዮኖች ይራቡ በነበሩባት ሀገር ሚሊዮኖች ራሳቸውን ከመመገብ አልፈው ለሌላውም ማምረትና ሀብት መፍጠር ደረጃ ላይ እንዲደርሱ ማስቻሉን አንክድም፡፡ ልማታዊ ባለሃብቶች በሀገር ውስጥም እየተፈጠሩ ከውጪም እየጎረፉ በከወኑት የኢንቨስትመንት ስራ ሀገሪቱ ተጨባጭ የለውጥ ማዕበል ውስጥ እየገባች መሆኑም እንዲሁ፡፡ ኢትዮጵያ ለረጅም ዘመናት የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች መብት የሚረገጥባት፣ ማንነታቸው የተካደበት፣ በንጉሳዊና ወታደራዊ አገዛዞች ህዝቦቿ በማንነታቸው፣ በእምነታቸውና በተፈጥሮአዊ መብታቸው ምክንያት ለስቃይ፣ እስራትና ስደት የተዳረጉባትም ነበረች፡፡ ይህን አስከፊ ስርአት ለመለወጥ ቀደም ሲል በተቀናጀም ባልተቀናጀም ሁኔታ የተለያዩ ትግሎች ሲደረጉ ቢቆዩም ኢህአዴግ ያደረገው መራር፣ የተቀናጀና የሰው ልጆችን መስዋእትነት ያስከፈለ ትግል ፍሬ አፍርቶ የፈጠረው አዲስ ስርአትና አዲስ ኢትዮጵያዊነት - ብሄር ብሄረሰቦች ሰብአዊ ፍጡርነታቸው የታወቀበት፣ ቋንቋና ባህላቸው ተከብሮ አደባባይ የወጡበት፣ እምነታቸው የተከበረበት፣ በልዩነታቸውና ህብረ ብሄርነታቸው ኢትዮጵያዊ የሆኑበት ስርዓት ሆኗል፡፡
ባለፉት 24 ዓመታት - ከደርግ ውድቀት በኋላ - ከልማት ስራውና ከድህነት ለመላቀቅ ከሚደረገው ጥረት እኩል ለእኩል ዴሞክራሲያዊ ስርዓት መገንባትና መልካም አስተደደር ማስፈን አማራጭ የሌለው፣ መተኪያ የሌለው አቅጣጫ መሆኑ
5
ተሰምሮበት ሲሰራበት ቢቆይም የተፈለገውን ያህል ውጤት ማምጣት ያልተቻለ እና ይልቁንም የኋልዮሽ እንዳይመልሰን በሚያሰጋ ደረጃ ላይ በመድረሱም ነው በገጸ በረከትነት መሻታችን፡፡ በእርግጥ የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ የተከናወኑ ተግባራት፣ የሴቶችና የሀይማኖት እኩልነት በተጨባጭ መረጋገጡ የተገኙ የለውጥ ውጤቶች ናቸው፡፡ በፌደራልና በክልል የመንግስት ተቋማት ሁሉ የአፈጻጸም ድርሻቸው ይለያይ እንጂ በሁሉም ቀልጣፋና ውጤታማ አሰራርን ለመዘርጋት የአሰራር ማሻሻያዎችና የተቋማዊ ለውጦች መሣሪያዎች መተግባራቸው መልካም አስተደዳርን ለማስፈን የተደረጉ ጥረቶችን የሚያመለክቱ መሆናቸውንም አልዘነጋንም ፡፡
የህዝቦች ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄ የመለሰ፣ በመረጡት መሪያቸው መተዳደርን መሠረት ያደረገ፣ በገቢያቸው የመወሰንና የመተዳደር ስልጣንን ያጎናፀፈ ነው፡፡ በአዲሱ አመት የምንሻውም የዴሞክራሲና የመልካም አስተዳደር ጥያቄያቸውም ሩቅ ሳይሄዱ፣ ማዕከላዊነት ላይ ሳያንጋጥጡ፣ ሳይጉላሉ በታችኛው የአስተዳደር እርከን እንዲመለሱልን ነው ፡፡
የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ህገመንግስት የህዝብ የስልጣን ሉአላዊነት የተገለጸበት፣ አላማዎቹና መሠረታዊ መርሆዎቹም ለዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታና ለመልካም አስተዳደር መስፈን መሠረትና ምንጭ የሆነ ህገመንግስት በሆነው ልክ በተግባርም መሬት እንዲይዝልን የምንፈልግበት የማያወላዳው ዘመን ላይ ነን፡፡
የመረጃ ነጻነት ተግባራዊነት ለዜጎች መሰረታዊ ዴሞክራሲያዊ መብቶች መከበርና ለሰብአዊ መብቶች መረጋገጥ መሰረት ነው፡፡ የሰዎች የመናገርና ሃሳብን የመግለጽ መብት የሰዎችን መረጃ የመፈለግ፣ የማግኘት፣ የማደራጀትና የማስተላለፍ መብትን ያካተተ ነው፡፡ እነዚህ መብቶች በሌሉበት ዜጎች መብታቸውን በትክክል ሊጠቀሙ፣ የሰብአዊና ዴሞክራሲያዊ የመብት ጥሰትን ሊያጋልጡ አይችሉም፡፡ ከዚህ ሌላ የመረጃ ነጻነት ለዴሞክራሲያዊ ስርአት ግንባታና ለመልካም አስተዳደር መስፈን ካለው ቁልፍ ሚና አንጻር መረጃን ለህዝብ ፍፁም ተደራሽ ማድረግ ይገባል፡፡ መረጃ ያለው ህብረሰተስብ በመንግስት አሰራር ላይ ግልጽ ግንዛቤ ስለሚኖረው ዴሞክራሲያዊ ተሳትፎው ይጎለብታል፡፡ ሙስናና በስልጣን አላግባብ የመጠቀም ብልሹ አሰራርን የሚያጋልጥ ኃይል ይሆናል፡፡ የመንግስት አሰራር ግልጽነት ከጎደለው ግን የህዝብ ተጠያቂነት የሌለው ፀረ-ዴሞክራሲያዊ አሰራር ይነግሳል፡፡ በመንግስት አሰራር ላይም ለሙስናና ብልሹ አሰራር የሚመቹ ጨለማዎች ይፈጥራሉ፡፡
መረጃ ያለው ዜጋ በካርዱ የስልጣን ውክልና የሰጠው አካል ተግባርና ኃላፊነቱን በአግባቡ እየተወጣ መሆኑን መከታተል ይችላል፡፡ መረጃ ያለው ዜጋ ዴሞክራሲያዊ መብቱን በመጠቀም ጥቅሙን የሚያስከብሩ ፖሊሲዎችና ውሳኔዎች እንዲወጡና እንዲፈፀሙ ግፊት ማድረግ ይችላል፡፡ በህገ-መንግስቱ የሰፈረው የዜጎች የመናገርና ሃሳብን የመግለጽ መብት ከመረጃ ነጻነት ውጭ በተሟላ ሁኔታ ተግባራዊ ሊሆን አይችልም፡፡ ስለሆነም የአዲሱ አመት መሻታችን ይህንንም ማካተቱ ስለእድገታችን ወሳኝ ይሆናል፡፡ ስልጣንን በውክልና የሰጠው ህዝብ ውክልና ተቀብሎ የሚያስተዳድረው መንግስት የተሰጠውን ሀብትና ስልጣን ለተገቢው ስራና አገልግሎት ማዋሉን ማየትና ማወቅ በአዲሱ አመት ይፈልጋል፡፡ ተወካዩም የወከለው ህዝብ ባዘዘውና በፈቀደው መንገድ መፈፀም ግድ ይለዋል፡፡ ይህን ለማረጋገጥ ግን የተወካዮች ስራዎችና አካሄዶች ሁሉ ለወካዮ/ ለህዝቡ/ ግልጽ መሆን አለባቸው፡፡ በኢትየጵያ ይህንኑ መሰረት በማድረግ የፌዴራሉም ሆነ የክልል ህገ-መንግስታት የመንግስትን ግልጽ አሰራርና ተጠያቂነት እንደ ዋነኛ መርሆ መደንገጋቸውን መዘንጋት አይገባም፡፡ በህገ-መንግስቱ የመንግስት አሰራር ለህዝብ ግልጽ መሆን እንዳለበት ማንኛውም ኃላፊና የህዝብ ተመራጭ ኃላፊነቱን ቢያጓድል ተጠያቂ እንደሚሆን ህዝብ በመረጠው አካል ላይ እምነት ሲያጣ ከቦታው ማንሳት እንደሚችልም ተደንግጓል፡፡ ይህ የኪራይ ሰብሳቢነት የፖለቲካ ኢኮኖሚ አረንቋን ለማድረቅ ሰፊ መሰረት የጣለ ነውና ለአዲሱ አመት በገጸ በረከትነት መሻታችን ተገቢነት ይኖረዋል ፡፡
6
ይህን ስንል ይህን ህገ-መንግስታዊ ድንጋጌ ተግባራዊ ለማድረግ ህገ-መንግስቱ ከፀደቀ ጀምሮ በተለይም ከተሃድሶው ወዲህ በፌደራልና የክልል ምክር ቤቶች በአስፈጻሚው ላይ ክትትልና ቁጥጥር የማድረግ፤ የአስፈጻሚውን የስራ አፈጻፀም ሪፖርት በቋሚ ኮሚቴዎች አማካይነትም የአስፈጻሚውን የሩብ ዓመት አፈጻፀም ገምግሞ ግብረ-መልስ የመስጠትና በአስፈጻሚው ላይ ከህብረተሰቡ የሚነሱ ጥያቄዎችና ጥቆማዎች በቋሚ ኮሚቴዎች ተመርምረው ምላሽ እንዲያገኙና ስራውን በአካል ተገኝቶ በመመልከት ሙስናና የሀብት ብክነት እንዳይኖር የሚያደርጉ አሠራሮች አልተዘረጉም ማለትም አይደለም፡፡ ይህንኑ ሂደት ይበልጥ ለማጎልበት በተለይም ወደ ታችኛዎቹ ምክር ቤቶች የሚዘልቅ የአቅም ግንባታ ሥራ በተጠናከረ መንገድ ማካሄድ በአዲሱ አመት ያስፈልጋል ማለታችን ነው፡፡
በመንግስት ተሻሚዎችና በመንግስት ተቋማት የሚታዩ የሙስና ጉዳዮችን የመከላከልና የማጣራት እርምጃዎች ራሱን በቻለ ተቛም በስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን እንዲመራ የተደረገውም የዚሁ የተጠያቂነትና ግልፅነት አሰራርን ለማስፈን የተያዘው ቁርጠኝነት አካል ስለሆነም ይመስለናልና ነው አጥብቀን መጠየቃችንና መሻታችን፡፡
ሁሉም ሥፍራ በአንድ ጊዜ መዝመት ስለማይቻል ይበልጥ ለችግር የተጋለጡትን መለየት የግድ ይላል፡፡ በመሆኑም ግብር ሰብሳቢ ድርጅቶች፣ በመሰረተ ልማት ግንባታ ላይ የተሰማሩ ተቋማት፣ ፈቃድ ሰጪ ተቋማት፣ በመሬት አስተዳደር ላይ የሚሰሩና በግንባታው ዘርፍ የተሰማሩት ግንባር ቀደሞቹ የችግሩ ሰለባዎች መሆናቸው ወይም የኪራይ ሰብሳቢነት ምንጮች መሆናቸው መለየታቸውን ድርጅቱ ነግሮናልና በአዲሱ አመት በተግባር እንጠብቀዋለን፡፡ አልያ የወጪ ንግድም ትራንስፎርሜሽንም ውሃ በላቸው ማለት ነው ፡፡

Saturday, 29 August 2015

GTP I የተፈፀመበት አግባብና ውጤቱ ከህዳሴያችን አንፃር የነበረው ፋይዳ!! ከብሩክ ከድር(part 2)



GTP I የተፈፀመበት አግባብና ውጤቱ ከህዳሴያችን አንፃር የነበረው ፋይዳ 
የመጀመሪያው ዙር ዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ፈጣን፣ ተከታታይና ፍትሃዊነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት ማስመዝገብና መዋቅራዊ ለውጥ ማምጣት ላይ ትኩረት አድርጎ ሲፈፀም የቆየ ሲሆን በርካታ አንፀባራቂ ውጤቶችም የተመዘገቡበትና ለሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሸን ዘመን እቅድ ጠቃሚ ልምዶች የተገኙበት ነበር፡፡ የሀገራችንን ህዳሴ ማረጋገጥ የምንችለው የተለጠጡና ወገብ የሚያጎብጡ እቅዶችን አቅደን በመተግበር ብቻ መሆኑን ታምኖበት ተግባራዊ በመደረጉ የጀመርነውን የዕድገት ግስጋሴ ከፍ ወዳለ ደረጃ ለማድረስ አስችሏል፡፡ በየደረጃው ከአመራር እስከ ህዝብ ድረስ በተደረጉ ጥልቀት ያላቸው ግምገማዎች እቅዱ በአግባቡ ተገምግሞ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል፡፡ የአፈፃፀም ግምገማው እንደሚያመለክተው ከተቀመጡ ግቦች ውስጥ ቀድመው የተሳኩ፣ በእቅዱ መሰረት የተሳኩ ግቦችና በተለያዩ ምክንያቶች በግባችን መሰረት ያልተሳኩ ግቦች መኖራቸውን መገምገም ተችሏል፡፡ በመላ ህዝባችን ከፍተኛ ንቅናቄ ታጅበን የፈፀምነው የመጀመሪያው 5 ዓመት እቅድ በብዙ መልኩ ስኬታማና ጠቃሚ ሀገራዊ ልምዶችም የተወሰዱበት እንደነበር መውሰድ ይቻላል፡፡  
የኢኮኖሚ ዕድገትና የህዝብ ተጠቃሚነትን ከማረጋገጥ አንፃር በአማካይ 10.1 በመቶ ዕድገት ማስመዝገብ የተቻለ ሲሆን በከተማችን በአማካይ በ15 በመቶ በላይ ፈጣን እድገት ተመዝግቧል፡፡  የኢኮኖሚ ዕድገቱ ከፍተኛ የስራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን ዓመታዊ አማካይ የነፍስ ወከፍ ገቢያችን በሀገር አቀፍ ደረጃ 700 ዶላር ደርሷል፡፡ በከተማችን የድህነት ምጣኔው በ1997 ከነበረበት 38.7 በመቶ በ2007 ወደ 22 በመቶ ዝቅ እንደሚል ተገምቷል፡፡ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ለውጥን ስንመለከት ከ2003-2006 ባሉት አራት ዓመታት የአገልግሎት ዘርፍ በ2003 64.18 % የነበረው በ2006 ወደ 62.6% ዝቅ ያለ ሲሆን የኢንዱስትሪ ዘርፍ ደግሞ ከ34.79 % ወደ 34.46% ከፍ ብሏል፡፡ ከዚህ በመነሳት መረዳት የሚቻለው የከተማው አብዛኛው ኢኮኖሚ የሚመነጨው ከአገልግሎት ዘርፍ መሆኑን ነው፡፡ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ለውጥ ማረጋገጥ ለእድገታችን ዘላቂነትና ወደ መካከለኛ ገቢ ኢኮኖሚ ለምናደርገው ጉዞ ወሳኝ በመሆኑ በመጀመሪያው ዙር የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ከተጠበቀው ይልቅ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር በከተማችን ወደ አገልግሎት ዘርፍ ያዘነበለ ነበር፡፡ የአገልግሎት ዘርፍ ማደግ በከተማችን ኢኮኖሚ ውስጥ ያለው ፋይዳ እንደተጠበቀ ሆኖ የኢኮኖሚውን ምርታማነት፣ የስራ ዕድልና የገበያ አቅም ለመፍጠር በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ልማት ላይ እመርታ ማምጣት የሞት የሽረት ጉዳይ ተደርጎ ሊወሰድ የሚገባው ነው፡፡  
የመሰረተ ልማት ፕሮግራሞችን በማሳካት ረገድ በኤሌክትሪክ ሀይል አቅርቦት፣ የመንገድ መሰረተ ልማት ዝርጋታ፣ የባቡር መንገድ ዝርጋታ፣ የቴሌኮሚኒኬሽን አገልግሎት በማዳራስ፣ ንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትን በማሳደግ ረገድ አመርቂ ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡ በማህበራዊ ልማት ረገድ የትምህርት ስርጭትና ሽፋን በማሳደግ እንዲሁም የጤና አገልግሎትን በማዳረስ ረገድ አንፀባራቂ ውጤቶች ተመዝገበዋል፡፡ የማስፈጸም አቅም ግንባታና ልማታዊ መልካም አስተዳደርን በማረጋገጥም ረገድ እንዲሁ ያለው የእቅድ ምዕራፍ ትርጉም ያለው ርቀት መሄድ ተችሏል፡፡ በአጠቃላይ አፈፃፀማችን የሚያመለክተው መካከለኛ ገቢ ያለው ዜጋና ከተማ ለመፍጠር የያዝነው ራዕይ ከተቀመጠው ጊዜ አስቀድመን ማሳካት እንደሚቻል ሲሆን አሁንም ትርጉም ባለው ደረጃ በከተማዋ ውስጥ የሚታየውን ድህነት ለመቅረፍ ቀን ከሌት መስራት የሚጠበቅብን መሆኑንንም መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ 
እነዚህንና ሌሎች ሀገራዊና ከተማ አቀፍ ስኬቶች እንደተጠበቁ ሆነው በሁሉም መስክ ያስመዘገብናቸው ለውጦች በመጠን ረገድ ጎልተው የወጡ ቢሆንም በሚፈለገው መጠን ጥራትን በማረጋገጥ ረገድ ክፍተቶች አሉ፡፡ ብቁ፣ ጥራት ያለውና ተወዳዳሪ ሆኖ ለመገኘት በየመስኩ ርብርብ ማድረግ ይጠይቀናል፡፡ የህዝብ ፍላጎት አዳጊ መሆንና ሞጋች ህብረተሰብ እየተፈጠረ ከመሄዱ አኳያ ይህንን ሁኔታ በተጨባጭ የተረዳ እንቅስቃሴ ሊኖረን ይገባል፡፡
የመጀመሪያው ዙር እቅድ ስኬታማ ሊሆን የቻለው የእቅዱ ፈፃሚ ሀይሎች በተደራጀ ንቅናቄ በመንቀሳቀሳቸው በተለይም ህዝቡ በእቅዶቹ ዙሪያ እየመከረ፣ አፈፃፀማቸውን እየገመገመ፣ ሲፈጸሙ በባለቤትነት የእቅዱ ፈፃሚ ሆኖ መረባረብ በመቻሉ ነው፡፡ ይህም በሁለተኛው ምዕራፍ እቅድ ይበልጥ እየተረጋጋጠ ሊሄድ የሚገባው ነው፡፡ የእቅዱ ዋነኛ ባህሪ መሰረታዊ የአመለካከት ለውጥና ሽግግርን (transformation) ማምጣት ላይ ትኩረት ያደረገ ከመሆኑ አኳያ የልማት ሀይሎች የነቃ ተሳትፎ ተኪ የሌለው ሚና ይጫወታል፡፡ ሁለተኛው ዕቅድ ረቂቅ ለህዝብ ውይይት በቀረበበት ወቅት በከተማችን በተከፈቱ የህዝብ መድረኮች መረዳት እንደተተቻለው ለቀጣዩ እቅድ ስኬታማነት ህዝቡ ከምንጊዜውም በላቀ ሁኔታ ድጋፉን የሰጠ መሆኑን ነው፡፡ በ10ኛው የድርጅታችን ኢህአዴግ ድርጅታዊ ጉባዔ ላይም ረቂቅ እቅድ ፀድቆ ከቀጣዩ በጀት ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ መደረግ የሚጀምር ሲሆን ለዚህ እቅድ ተፈፃሚነት በየደረጃው ያለ አመራራችንና መዋቅራችን በከፍተኛ ወኔና እልህ መንቀሳቀስ ይጠበቅባቸዋል፡፡   
GTP II ከህዳሴያችን አንፃር ምን ትርጉም ይኖረዋል?
የልማታዊ ዴሞክራሲያዊ መስመራችን በተሞክሮነት የሚወስዳቸው የምስራቅ ኢስያ ፈጣን ኢኮኖሚ ያስመዘገቡ ሀገራት (Asian Tigers) ወይም The Four Asian Dragons የምንላቸው ታይዋን፣ ደቡን ኮሪያ፣ ሆንግ ኮንግና ሲንጋፖር ከ1960ዎቹ እስከ 1990ዎቹ መጨረሻ ድረስ ፈጣንና ተከታታይነት ያለው አስደናቂ እድገት በልማታዊ መንገድ ማስመዘገብ ችለዋል፡፡ ህዝባቸውን ከድህነት በማውጣት ዛሬ ሀገራቱ በዓለም ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ መፍጠር የሚችሉ ሀገራት ሆነዋል፡፡ ደቡብ ኮሪያና ታይዋን በአይቲ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ በዓለም ቀዳሚ ሀገራት ናቸው፡፡ ሆንግ ኮንግና ሲንጋፖር ደግሞ በዓለም በመሪነት የሚቀመጡ የፋይናንስ ማዕከላት መሆን ችለዋል፡፡ እነዚህ ሀገራት እዚህ ደረጃ ላይ መድረስ የቻሉት በተከታታይ ሊያሰሩ የሚችሉ እቅዶችን አቅደው፣ ወገባቸውን ጠበቅ አድርገው መፈጸም በመቻላቸውና ልማታዊ አመራር ጥበብን በመከተላቸው ነው፡፡     
ከዓለም ፈጣን ኢኮኖሚዎች ውስጥ አንዱ የቻይና ኢኮኖሚ ነው፡፡ በዓመታዊ ጠቅላላ ምርት ሁለተኛው የዓለም ትልቁ ኢኮኖምም ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ ባለፉት 30 ዓመታት ኢኮኖሚያቸው በአማካይ በ10 መቶ ሲያድግ ቆይቷል፡፡ ይህም ሆኖ ግን እንደ ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) ሪፖርት መሰረት ከድህነት ወለል በታች 6.1 በመቶ ህዝብ ይኖርባታል፡፡ ቻይና ከ1953 ጀምሮ እስከ 2015 ድረስ 12 ጊዜ ያህል ተከታታይ የ5 ዓመታት እቅድ ስትተገብር ቆይታለች፡፡ በዚህ ውስጥ ከ1958-1962 ድረስ የነበረው ሁለተኛው ዙር እቅድ ታላቁ እመርታዊ ለውጥ የሚል ስያሜ ነበረው፡፡ ሌሎች በመሃል ያሉ የስትራቴጂክ እቅድ ዓመታት የየራሳቸው ስያሜና ልዩ የትኩረት ማዕከላት ነበሯቸው፡፡ በእነዚህ ዓመታት ውስጥ በተከታታይ ሲተገበር በነበረው እቅድ ውስጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ ሀገሪቱን ወደ ኢንዱስትሪ ማዕከልነት በመቀየር፣ በድህነት ውስጥ ያለን ህዝብ የማውጣትና ሀገሪቱን የማዘመን ስራዎች ትኩረት ተሰጥቷቸው ስለተመሩ ዛሬ ቻይናን ባለ ግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤትነት አምጥተዋል፡፡     
እኛ የመጀመሪያውን ዙር የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ በስኬት አጠናቀን ወደ ሁለተኛው ስንሄድ የወጣነው ደገት ቢኖርም አሁንም አሁንም እጅግ ብዙ ያልወጣነው ደገት መኖሩን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ ህዳሴያችን የተከታታይ ትውልዶች ትግልን የሚጠይቅና ጉዞው ያለምንም መሰነካከል ፍጥነቱን ጠብቆ እንዲቀጥል ማድረግ ይገባል፡፡ ከድቅድቅ ጨለማ ወጥተን የብርሃን ዘመንን ለማምጣት የምስራቅ ኢሲያ ሀገራት ያለፉበትን ውጣ ውረድ፣ የረገጡት ድንጋይ መርገጥና የከፈሉትን መሰዋዕትነት ይበልጥ መክፈል ይጠይቃል፡፡ ዛሬ የጀመርነው የህዳሴ ጉዞ የነገዋን ኢትዮጵያ በማበጀት ሂደት ውስጥ ያለውን ከፍተኛ ትርጉም በመረዳት በላቀ እልህና ወኔ ለቀጣዩ ተልዕኮ በየመስኩ ራስን ማዘጋጀት ያስፈልጋል፡፡
  
 

የኢትዮጵያ ህዳሴና GTP II ( GTP I የተፈፀመበት አግባብና ውጤቱ ከህዳሴያችን አንፃር የነበረው ፋይዳ ከብሩክ ከድር (part 2)



GTP I የተፈፀመበት አግባብና ውጤቱ ከህዳሴያችን አንፃር የነበረው ፋይዳ 
የመጀመሪያው ዙር ዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ፈጣን፣ ተከታታይና ፍትሃዊነት ያለው የኢኮኖሚ ዕድገት ማስመዝገብና መዋቅራዊ ለውጥ ማምጣት ላይ ትኩረት አድርጎ ሲፈፀም የቆየ ሲሆን በርካታ አንፀባራቂ ውጤቶችም የተመዘገቡበትና ለሁለተኛው የዕድገትና ትራንስፎርሜሸን ዘመን እቅድ ጠቃሚ ልምዶች የተገኙበት ነበር፡፡ የሀገራችንን ህዳሴ ማረጋገጥ የምንችለው የተለጠጡና ወገብ የሚያጎብጡ እቅዶችን አቅደን በመተግበር ብቻ መሆኑን ታምኖበት ተግባራዊ በመደረጉ የጀመርነውን የዕድገት ግስጋሴ ከፍ ወዳለ ደረጃ ለማድረስ አስችሏል፡፡ በየደረጃው ከአመራር እስከ ህዝብ ድረስ በተደረጉ ጥልቀት ያላቸው ግምገማዎች እቅዱ በአግባቡ ተገምግሞ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል፡፡ የአፈፃፀም ግምገማው እንደሚያመለክተው ከተቀመጡ ግቦች ውስጥ ቀድመው የተሳኩ፣ በእቅዱ መሰረት የተሳኩ ግቦችና በተለያዩ ምክንያቶች በግባችን መሰረት ያልተሳኩ ግቦች መኖራቸውን መገምገም ተችሏል፡፡ በመላ ህዝባችን ከፍተኛ ንቅናቄ ታጅበን የፈፀምነው የመጀመሪያው 5 ዓመት እቅድ በብዙ መልኩ ስኬታማና ጠቃሚ ሀገራዊ ልምዶችም የተወሰዱበት እንደነበር መውሰድ ይቻላል፡፡  
የኢኮኖሚ ዕድገትና የህዝብ ተጠቃሚነትን ከማረጋገጥ አንፃር በአማካይ 10.1 በመቶ ዕድገት ማስመዝገብ የተቻለ ሲሆን በከተማችን በአማካይ በ15 በመቶ በላይ ፈጣን እድገት ተመዝግቧል፡፡  የኢኮኖሚ ዕድገቱ ከፍተኛ የስራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን ዓመታዊ አማካይ የነፍስ ወከፍ ገቢያችን በሀገር አቀፍ ደረጃ 700 ዶላር ደርሷል፡፡ በከተማችን የድህነት ምጣኔው በ1997 ከነበረበት 38.7 በመቶ በ2007 ወደ 22 በመቶ ዝቅ እንደሚል ተገምቷል፡፡ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ለውጥን ስንመለከት ከ2003-2006 ባሉት አራት ዓመታት የአገልግሎት ዘርፍ በ2003 64.18 % የነበረው በ2006 ወደ 62.6% ዝቅ ያለ ሲሆን የኢንዱስትሪ ዘርፍ ደግሞ ከ34.79 % ወደ 34.46% ከፍ ብሏል፡፡ ከዚህ በመነሳት መረዳት የሚቻለው የከተማው አብዛኛው ኢኮኖሚ የሚመነጨው ከአገልግሎት ዘርፍ መሆኑን ነው፡፡ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ለውጥ ማረጋገጥ ለእድገታችን ዘላቂነትና ወደ መካከለኛ ገቢ ኢኮኖሚ ለምናደርገው ጉዞ ወሳኝ በመሆኑ በመጀመሪያው ዙር የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ከተጠበቀው ይልቅ የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር በከተማችን ወደ አገልግሎት ዘርፍ ያዘነበለ ነበር፡፡ የአገልግሎት ዘርፍ ማደግ በከተማችን ኢኮኖሚ ውስጥ ያለው ፋይዳ እንደተጠበቀ ሆኖ የኢኮኖሚውን ምርታማነት፣ የስራ ዕድልና የገበያ አቅም ለመፍጠር በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ልማት ላይ እመርታ ማምጣት የሞት የሽረት ጉዳይ ተደርጎ ሊወሰድ የሚገባው ነው፡፡  
የመሰረተ ልማት ፕሮግራሞችን በማሳካት ረገድ በኤሌክትሪክ ሀይል አቅርቦት፣ የመንገድ መሰረተ ልማት ዝርጋታ፣ የባቡር መንገድ ዝርጋታ፣ የቴሌኮሚኒኬሽን አገልግሎት በማዳራስ፣ ንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትን በማሳደግ ረገድ አመርቂ ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡ በማህበራዊ ልማት ረገድ የትምህርት ስርጭትና ሽፋን በማሳደግ እንዲሁም የጤና አገልግሎትን በማዳረስ ረገድ አንፀባራቂ ውጤቶች ተመዝገበዋል፡፡ የማስፈጸም አቅም ግንባታና ልማታዊ መልካም አስተዳደርን በማረጋገጥም ረገድ እንዲሁ ያለው የእቅድ ምዕራፍ ትርጉም ያለው ርቀት መሄድ ተችሏል፡፡ በአጠቃላይ አፈፃፀማችን የሚያመለክተው መካከለኛ ገቢ ያለው ዜጋና ከተማ ለመፍጠር የያዝነው ራዕይ ከተቀመጠው ጊዜ አስቀድመን ማሳካት እንደሚቻል ሲሆን አሁንም ትርጉም ባለው ደረጃ በከተማዋ ውስጥ የሚታየውን ድህነት ለመቅረፍ ቀን ከሌት መስራት የሚጠበቅብን መሆኑንንም መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ 
እነዚህንና ሌሎች ሀገራዊና ከተማ አቀፍ ስኬቶች እንደተጠበቁ ሆነው በሁሉም መስክ ያስመዘገብናቸው ለውጦች በመጠን ረገድ ጎልተው የወጡ ቢሆንም በሚፈለገው መጠን ጥራትን በማረጋገጥ ረገድ ክፍተቶች አሉ፡፡ ብቁ፣ ጥራት ያለውና ተወዳዳሪ ሆኖ ለመገኘት በየመስኩ ርብርብ ማድረግ ይጠይቀናል፡፡ የህዝብ ፍላጎት አዳጊ መሆንና ሞጋች ህብረተሰብ እየተፈጠረ ከመሄዱ አኳያ ይህንን ሁኔታ በተጨባጭ የተረዳ እንቅስቃሴ ሊኖረን ይገባል፡፡
የመጀመሪያው ዙር እቅድ ስኬታማ ሊሆን የቻለው የእቅዱ ፈፃሚ ሀይሎች በተደራጀ ንቅናቄ በመንቀሳቀሳቸው በተለይም ህዝቡ በእቅዶቹ ዙሪያ እየመከረ፣ አፈፃፀማቸውን እየገመገመ፣ ሲፈጸሙ በባለቤትነት የእቅዱ ፈፃሚ ሆኖ መረባረብ በመቻሉ ነው፡፡ ይህም በሁለተኛው ምዕራፍ እቅድ ይበልጥ እየተረጋጋጠ ሊሄድ የሚገባው ነው፡፡ የእቅዱ ዋነኛ ባህሪ መሰረታዊ የአመለካከት ለውጥና ሽግግርን (transformation) ማምጣት ላይ ትኩረት ያደረገ ከመሆኑ አኳያ የልማት ሀይሎች የነቃ ተሳትፎ ተኪ የሌለው ሚና ይጫወታል፡፡ ሁለተኛው ዕቅድ ረቂቅ ለህዝብ ውይይት በቀረበበት ወቅት በከተማችን በተከፈቱ የህዝብ መድረኮች መረዳት እንደተተቻለው ለቀጣዩ እቅድ ስኬታማነት ህዝቡ ከምንጊዜውም በላቀ ሁኔታ ድጋፉን የሰጠ መሆኑን ነው፡፡ በ10ኛው የድርጅታችን ኢህአዴግ ድርጅታዊ ጉባዔ ላይም ረቂቅ እቅድ ፀድቆ ከቀጣዩ በጀት ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ መደረግ የሚጀምር ሲሆን ለዚህ እቅድ ተፈፃሚነት በየደረጃው ያለ አመራራችንና መዋቅራችን በከፍተኛ ወኔና እልህ መንቀሳቀስ ይጠበቅባቸዋል፡፡   
GTP II ከህዳሴያችን አንፃር ምን ትርጉም ይኖረዋል?
የልማታዊ ዴሞክራሲያዊ መስመራችን በተሞክሮነት የሚወስዳቸው የምስራቅ ኢስያ ፈጣን ኢኮኖሚ ያስመዘገቡ ሀገራት (Asian Tigers) ወይም The Four Asian Dragons የምንላቸው ታይዋን፣ ደቡን ኮሪያ፣ ሆንግ ኮንግና ሲንጋፖር ከ1960ዎቹ እስከ 1990ዎቹ መጨረሻ ድረስ ፈጣንና ተከታታይነት ያለው አስደናቂ እድገት በልማታዊ መንገድ ማስመዘገብ ችለዋል፡፡ ህዝባቸውን ከድህነት በማውጣት ዛሬ ሀገራቱ በዓለም ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ መፍጠር የሚችሉ ሀገራት ሆነዋል፡፡ ደቡብ ኮሪያና ታይዋን በአይቲ ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ በዓለም ቀዳሚ ሀገራት ናቸው፡፡ ሆንግ ኮንግና ሲንጋፖር ደግሞ በዓለም በመሪነት የሚቀመጡ የፋይናንስ ማዕከላት መሆን ችለዋል፡፡ እነዚህ ሀገራት እዚህ ደረጃ ላይ መድረስ የቻሉት በተከታታይ ሊያሰሩ የሚችሉ እቅዶችን አቅደው፣ ወገባቸውን ጠበቅ አድርገው መፈጸም በመቻላቸውና ልማታዊ አመራር ጥበብን በመከተላቸው ነው፡፡     
ከዓለም ፈጣን ኢኮኖሚዎች ውስጥ አንዱ የቻይና ኢኮኖሚ ነው፡፡ በዓመታዊ ጠቅላላ ምርት ሁለተኛው የዓለም ትልቁ ኢኮኖምም ተደርጎ ይወሰዳል፡፡ ባለፉት 30 ዓመታት ኢኮኖሚያቸው በአማካይ በ10 መቶ ሲያድግ ቆይቷል፡፡ ይህም ሆኖ ግን እንደ ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (IMF) ሪፖርት መሰረት ከድህነት ወለል በታች 6.1 በመቶ ህዝብ ይኖርባታል፡፡ ቻይና ከ1953 ጀምሮ እስከ 2015 ድረስ 12 ጊዜ ያህል ተከታታይ የ5 ዓመታት እቅድ ስትተገብር ቆይታለች፡፡ በዚህ ውስጥ ከ1958-1962 ድረስ የነበረው ሁለተኛው ዙር እቅድ ታላቁ እመርታዊ ለውጥ የሚል ስያሜ ነበረው፡፡ ሌሎች በመሃል ያሉ የስትራቴጂክ እቅድ ዓመታት የየራሳቸው ስያሜና ልዩ የትኩረት ማዕከላት ነበሯቸው፡፡ በእነዚህ ዓመታት ውስጥ በተከታታይ ሲተገበር በነበረው እቅድ ውስጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ ሀገሪቱን ወደ ኢንዱስትሪ ማዕከልነት በመቀየር፣ በድህነት ውስጥ ያለን ህዝብ የማውጣትና ሀገሪቱን የማዘመን ስራዎች ትኩረት ተሰጥቷቸው ስለተመሩ ዛሬ ቻይናን ባለ ግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤትነት አምጥተዋል፡፡     
እኛ የመጀመሪያውን ዙር የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ በስኬት አጠናቀን ወደ ሁለተኛው ስንሄድ የወጣነው ደገት ቢኖርም አሁንም አሁንም እጅግ ብዙ ያልወጣነው ደገት መኖሩን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ ህዳሴያችን የተከታታይ ትውልዶች ትግልን የሚጠይቅና ጉዞው ያለምንም መሰነካከል ፍጥነቱን ጠብቆ እንዲቀጥል ማድረግ ይገባል፡፡ ከድቅድቅ ጨለማ ወጥተን የብርሃን ዘመንን ለማምጣት የምስራቅ ኢሲያ ሀገራት ያለፉበትን ውጣ ውረድ፣ የረገጡት ድንጋይ መርገጥና የከፈሉትን መሰዋዕትነት ይበልጥ መክፈል ይጠይቃል፡፡ ዛሬ የጀመርነው የህዳሴ ጉዞ የነገዋን ኢትዮጵያ በማበጀት ሂደት ውስጥ ያለውን ከፍተኛ ትርጉም በመረዳት በላቀ እልህና ወኔ ለቀጣዩ ተልዕኮ በየመስኩ ራስን ማዘጋጀት ያስፈልጋል፡፡
  
  

የኢትዮጵያ ህዳሴና GTP II ከብሩክ ከድር (part 1)




የኢትዮጵያ ሚሊኒየም (2000 ዓ.ም) ዋዜማ አዲሱን ሺህ ዓመት ስንቀበል በሚሊኒየም አደራሽ በተደረገ መርሃ ግብር ላይ ታላቁ መሪያችን መለስ ዜናዊ ‹‹መጪው ዘመን የኢትዮጵያ ህዳሴ ይሆናል!!›› ማለታቸው ይታወሳል፡፡ ያሳለፍነው ሚሊኒየም ሀገራችን በአንድ ወቅት ከዓለም ታላላቅ ስልጣኔዎች መካከል የነበረችበትና በሂደትም ፀጋዋን በአግባቡ መጠቀም ባለመቻሏና ብዝኃነቷን በብቃት መምራት የሚያስችል ሁኔታ ባለመፈጠሩ ቀደሞ የነበራት ዝናና ገናናነት በሂደት በማሽቆልቆል የተተካበት ሁኔታም ተፈጥሯል፡፡ በማያቋርጥ የኋሊዮሽ ጉዞ ያለፈችበት ወቅትም ነበር፡፡
ታላቁ መሪያችን መለስ ዜናዊ በሚሊኒየም አደራሽ ባደረጉት ንግግር ‹‹ላለፍንበት ሁኔታ ተጠያቂዎቹ እኛና እኛው ብቻ ነን፡፡›› በሚል ያስቀመጡት ሀሳብ የሚያመለክተን የተሻለች ሀገርን ለቀጣዩ ትውልድ ማስረከብ እስካልቻልን ድረስ የትውልድ ተጠያቂነትም የማይቀር እውነታ መሆኑን ነው፡፡ ሀገራችን ወደ ቀድሞ ገናናነት ዘመኗ ዳግም የመመለስ ጉዞ የህዳሴ (renaissance) እቅዳችን መነሻም ከዚህ እልህና ቁጭት የሚነሳ ነው፡፡     
የኢትዮጵያ ህዳሴ የሚለው ፅንሰ ሀሳብ በተግባርም ሆነ በንድፈ ሀሳብ ደረጃ በሀገር ውስጥም ይሁን በውጪው ማህበረሰብ ዘንድ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተለመደ የመጣ ጉዳይ ሆኗል፡፡ ይህ ጽንሰ ሀሳብ ለኢትዮጵያዊያን ያለው ትርጉም ላቅ ያለና ነገን በዛሬ የመስራት ያህል ነው፡፡ በአንድ ወቅት በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ ለነበረችና ዜጎቿ በድህነትና በከፋ ረሃብ ሲማቅቁ የነበሩባትን ሀገር ወደ ከፍታ ዘመን የሚመልስ ታላቅ ሀገራዊ ፍኖተ ካርታ (roadmap) ነው፡፡ የኢትዮጵያ ህዳሴ ማለት በዓለም አደባባይ ተሰሚነታችን ጎልቶ የሚወጣበትን ታሪክ በጋራ ጥረታችን የምንገነባባት ቁልፍ የርብርብ ማዕከል ነው፡፡ይህም በመሆኑ በዛሬውና በነገው ትውልድ መካከል ለሀገራዊ ቅብብል ድልድይ ሆኖ የሚያገለግል የርብርብ አጀንዳችንም ጭምር ተደርጎ ይወሰዳል፡፡   
የኢትዮጵያ ህዳሴ መሰረት የተጣለው መቼ ነው?
የሀገራችን ህዳሴ መሰረት የተጣለው መቼ ነው ካልን ለሁለት ወቅቶች ከፍተኛ ትርጉም መስጠት ያስፈልጋል፡፡ ቀዳሚው ወቅት አፋኙ የደርግ ስርዓት በህዝባዊ ትግል የተገረሰሰበት ወቅት ነው፡፡ የድህነት ዘበኛ፣ የብዝሃነት ጠላት፣ የትምክህተኝነት ወኪልና የግዛት አንድነት አቀንቃኝ የነበረው ደርግ በከፋና እልህ አስጨራሽ ትግል መወገዱ ለሀገራችን ህዳሴ ቀዳሚው መሰረት ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል፡፡ ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ የህዳሴያችን መሰረት ይበልጥ የተጣለውና በአስተማማኝ መልኩ ነጥሮ የወጣው የዛሬ አስራ አራት ዓመት የተሃዳሶው መስመር ጠርቶ በወጣበት ወቅት ነው፡፡ ምንም እንኳ በህዝባዊ የትጥቅ ትግል ደርግ ከተወገደ በኋላ ሀገራችን ፊቷን ወደ ሰላምና መረጋገት፣ ልማትና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ አዙራ የነበረ ቢሆንም የመድረኩን ባህሪ በትክክል ተረድቶ የጠራ አሰላለፍ ያለው ትግል በማድረግ በኩል ግን የውስጠ ድርጅት አደጋዎች አጋጥመው እንደነበር ይታወሳል፡፡ በወቅቱ ያጋጠመውን ውስጣዊ የመበስበስ አደጋ በከፍተኛ ብስለት ያለምንም ደም መፋሰስ በሀሳብ ትግል አሸናፊነት በመጠናቀቁ በወሳኝ መልኩ የሀገራችን ህዳሴ መሰረት እንዲጣል አድርጓል፡፡  
 የሀገራችን ቁልፍ ጠላት ከድህነት በላይ ሊሆን እንደማይችል፣ ትግላችን በኪራይ ሰብሳቢነትና በልማታዊነት መካከል እንደሆነ፣ ሀገራችንን ከከፋ ድህነትና ኋላ ቀርነት አውጥተን ወደ ብልፅግና ዘመን ለማምራት ብሔራዊ መግባባትን በመፍጠር በተደራጀ የህዝብ ተሳትፎ መንቀሳቀስ እንደሚገባን ያስቀመጥበት ወቅት ነበር፡፡ ባለፉት የተሃዳሶው ዘመናት በወቅቱ የተጠቀመጡት የመታገያ አጀንዳዎች ተለቅመው መተግባር ጀምረዋል፣ ፍሬያቸውም በመታየት ላይ ነው፡፡ ዛሬ ላይ ሆነን ያለፉት የተሃድሶው ዓመታት ስናይ ሀገራችንን ከድህነት አረንቋ ለማውጣት የሞት የሽረት ጉዳይ ማድረግ እስካልቻልን ድረስ ሀገራዊ ህልውናችን ጭምር አደጋ ላይ እንደሚወድቅ የተቀመጠው አቅጣጫ ትክክለኛና ወደፊት የምናደርገውን ግስጋሴ  ያፈጠነ እንደነበር መውሰድ ይቻላል፡፡        

የኢትዮጵያ ህዳሴ ማረጋገጫዎች 
ሀገራችን ህዳሴዋን እያረጋገጠች ስለመሆኑ በርካታ ማሳያዎች ማቅረብ ይቻላል፡፡ ከብዙ ማሳያዎች ውስጥ ግን ከፍተኛ ትርጉም ያላቸውን የተወሰኑ ጉዳዮች በማንሳት የኢትዮጵያ ህዳሴ በየመስኩ እየተረጋገጠ ስለመሆኑ ማሳየት ይቻላል፡፡ ቀዳሚው የህዳሴያችን ማረጋገጫ በወሳኝ ሀገራዊ ጉዳዮች እየተፈጠረ ያለው ብሔራዊ መግባባት ነው፡፡ ከወርቃማው ታሪካችን እንደምንገነዘበው የሀገራችን ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በጋራ ጉዳይ ቆመው በአንድነት ጠላትነት ፋሽስት ጣሊያንን የመከቱበት የአድዋ ድልን ያህል አሁንም በድህነት ላይ በጋራ ለመዝመት የተነሳሳንበት ወቅት ተፈጥሯል፡፡ ብሔራዊ መግባባት በጥቃቅን ጉዳዮች ላይ ጭምር በጋራ መቆምን የግድ የሚል ፍልስፍና ሳይሆን በወሳኝ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ባጋራ መቆምን የሚጠይቅ አስተሳሰብ ነው፡፡ ከዚህ አንፃር ከታየ በህገ መንግስታችን፣ በጋራ ጠላቶቻችን ዙሪያ እየፈጠርነው ያለ መግባባት ህዳሴያችንን እውን ከማድረግ አኳያ የራሳቸው ከፍተኛ ፋይዳ አላቸው፡፡
ምንም እንኳ አሁንም በከፋ ድህነት ውስጥ የሚቃቀው ህዝባችን ቁጥር ቀላል የሚባል ባይሆንም ባለፉት ሁለት አስር ተከታታይ ዓመታት ሀገራችን ሚሊዮኖችን ከአስከፊ ድህነት ውስጥ ማውጣት ችላለች፡፡ በምግብ እህል ራሳችንን እስከመቻል ደርሰናል፡፡ ትልልቅ ሀገራዊ ፕሮጀክቶችን በራሳችን ወጪ መገንባት የሚያስችል ሀገራዊ አቅምም ፈጥረናል፡፡ ገፅታችን በውስጥ እየተገነባ ሲመጣ በውጭ ግንኙነት ረገድ ተሰሚነታችን እየጨመረ መጥቷል፡፡ ከምስራቅ ኢስያ ሀገራት ልምድ ተነስተን ስናይ በተለያዩ ምክንያቶች የተሰደደው ዲያስፖራ ወደ ሀገሩ ተመልሶ የለውጥ አካል መሆን መቻሉም አንዱ የህዳሴያችን ምልክት ተደርጎ ይወሳዳል፡፡ 
እነዚህና የመሳሰሉት ማሳያዎችን ስንመለከት የሀገራችን የህዳሴ ጉዞ ተጨባጭ በሆነ መልኩ እየታየ፣ እየጎመራ፣ ወይም በተስፋ ሰጪ ምህዋር ውስጥ የሚገኝ መሆኑን ነው፡፡    

Monday, 24 August 2015

የኢትዮጵያ ወጣቶችና የመሰረታዊ ለውጥ ትግላቸው part 2

በማስከተልም ዋለልኝ ህዝባዊ መንግስት ይመስረት ብሎ ሞገተ። ምን ዓይነት ህዝባዊ መንግስት? በሚለውም ላይ «እውነተኛ ህዝባዊ መንግስት፤ ሁሉም ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች እኩል የሚሳተፉበትና ህዝቦቹ የየራሳቸውን ቋንቋ፣ ባህል፣ ታሪክ የሚጠብቁበትና የሚያሳድጉበት መንግስት ይመስረት» (ዋለልኝ; 1961፤3፡) በማለት ታግሎ መስዋዕት ሆኗል።ዋለልኝን እንደ አብነት ጠቀስን እንጂ በሺዎች የሚቆጠሩ ፊደል ቀመስ የለውጥ ንቅናቄው ግንባር ቀደም ወጣቶች በርካታ ነበሩ፡፡
በ1960ዎቹ የነበረው የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ንቅናቄና በየአካባቢው አርሶ አደሩ ያቀጣጠለው ፀረ-ፊውዳል ንቅናቄ በ1966 የንጉሱን ስልጣን ገረሰሰ፡፡ የህዝቡ ንቅናቄ የፊውዳሉን ስርዓት ቢያስወግድም የአቢዮቱ አንቀሳቃሾች በአግባቡ የተደራጁ ስላልነበሩ በወቅቱ የተደራጀ አቅም የነበረው ወታደራዊ ስርዓት ተቆጣጥሮ የህዝቡን ንቅናቄ ለመጨፍለቅ ሲል ያለምንም ደም ኢትዮጵያ ትቅደም!! ከሚለው አንስቶ ተከታታይ አፋኝ መፈክሮችን ቀርፆ በአስርሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን በቀይ ሽብር ዘመቻ ጨፈጨፈ፡፡ ሠላማዊ ትግል ለውጥ እንደማያመጣ የተገነዘቡት የለውጥ ኃይሎች በብሄራዊም ሆነ በህብረ-ብሔራዊ መልክ ትግላቸውን አቀጣጠሉ፡፡በትግል መስመር ጥራትና በአፈፃፀም ቁርጠኝነት ስርዓቱን ተቃውመው የተንቀሳቀሱ ሁሉ ለፀረ-ደርግ ትግሉ እኩል አስተዋጽኦ ነበራቸው ለማለት ያስቸግራል፡፡ ሆኖም ከተቃውሞ ጀምሮ እስከ ለየለየት የጦር ሜዳ ውጊያ በማምራት 17 ዓመትን በወሰደ ከባድ መስዋዕትነት ለዘመናት በህዝቦች ጫንቃ ላይ ተንጠላጥሎ የኖረው የፊውዳልና ቅሪት ፊውዳል እንዲሁም አምባገነኑ የደርግ ስርዓት እስከ አፈና መዋቅሩ ፈራረሰ፡፡ በዚህም የኢትዮጵያ ህዝቦች መሰረታዊ የልማት፣ የዴሞክራሲና ዘላቂነት ያለው ሠላምን ለማረጋገጥ የተደረገው ስር ነቀል አብዮታዊ ፍልሚያ የመጀመሪያው ምዕራፍ በህዝቦች ንቁ ተሳትፎ በድል ተጠናቀቀ፡፡ የዚህ የጦር ሜዳ ፍልሚያና ክቡር መስዋዕትነት እንዲሁም ድል ግንባር ቀደም ተዋናኝ የያኔ ዘመን ወጣቶች የዛሬ አንጋፋዎች ድርሻ ከፍተኛ ነበር፡፡
ግንቦት 20/ 1983 ዓ.ም የተገኘው ህዝባዊ ድል የዘመናት የህዝቦች ተጋድሎ ድል የተቀናጀበት የአብዮቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ እንጂ የመጨረሻ አልነበረም፡፡ የህዝቦች ትግል ወደ ኋላ ሳይል አስተማማኝ መሰረት የሚይዘው ህዝቦች አንግበዋቸው ለተነሷቸው የሠላም፣ የዴሞክራሲና የልማት ጥያቄዎች ህጋዊ ዋስትና የሚሰጥ ልማታዊና ዴሞክራሲያዊ ህገ-መንግስት በህዝቦች ተሳትፎ መረቀቅና መጽደቅ ነበረበት፡፡ ይህ የመሰረታዊ ለውጥ ንቅናቄው ሁለተኛው ቁልፍ ምዕራፍ ነበር፡፡ ህዝባዊና ቀጣይነት ያለው ህገ-መንግስት አርቅቆና በህዝብ የነቃ ተሳትፎ በማጽደቅ ወደ ዘላቂ ሠላም፣ ልማትና ዴሞክራሲ ጉዞ ለማምራት ሁሉም ያገባናል ባዮች በሂደቱ፣ ከመነሻ እስከ መዳረሻው ሊሳተፉ ይገባ ነበር፡፡ በመሆኑም በኢህአዴግ የሚመራው ጊዜያዊ መንግስት የነበረውን ስርዓት “አስወግጃለሁ፤ ስልጣን ይገባኛል” ሳይል አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ አሉ የሚባሉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች እና ተሰሚነት ያላቸው ግለሰቦች ጭምር የተሳተፉበት የሽግግር መንግስት ተመሰረተ:: በዚህ ጊዜ ውስጥ ለዘመናት ተንሰራፍቶ የቆየውን ህገ-ወጥነት በማጽዳት፣ ለሠላምና መረጋጋት እንዲሁም ለህዝብ ነፃና የተመቸ እንቅስቃሴ እንቅፋት የነበሩ ህገ ወጦችና ሽፍቶች ህዝቡን ባሳተፈ መልኩ በህግ ስር እንዲውሉ ህዝቡ በሠላማዊ መልኩ በነፃነት እንዲንቀሳቀስ ሰፊ ስራ ተከናወነ፡፡ በሽግግር መንግስቱ አማካኝነት የህገ-መንግስት አርቃቂ ኮሚሽን ተዋቀረ፡፡ ኮሚሽኑ ባዘጋጀው መነሻ ሃሳብ ላይ ከ16 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ህዝቦች በረቂቅ ሰነዱ ተወያይተው ማስተካከያና ማሻሻያ ሃሳብ ካቀረቡ በኋላ ወኪሎቹ የበለጠ ተወያይተው እንዲያፀድቁለት፣ በዴሞክራሲያዊ ምርጫ ወኪሎችን መርጦ በተወካዮች አማካኝነት ቀናትን በወሰደ ውይይት ልማታዊና ዴሞክራሲያዊ ህገ-መንግስት ህዳር 1987 ፀደቀ፡፡ ከላይ የተጠቀሱት ስኬታማ ተግባራት የተከናወኑ በዛን ዘመን የነበሩ ወጣቶችና የአሁን ዘመን ጎልማሶች ግንባር ቀደም ተዋናኝነት ነበር፡፡
ህገ-መንግስቱ ከሠላም አኳያ በአገራችን አስተማማኝና ዘላቂ ሠላም የሚረጋገጥባቸው አንቀፆች አስቀምጧል፡፡ የህዝቦች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብት እንዲከበር፣ የዘመናት የግጭት አንድ ምክንያት ሆኖ የቆየው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች የራስን እድል በራስ የመወሰን መብት እስከመገንጠል እውቅና ሰጠ፡፡ በመሆኑም ከብዙዎቹ የዴሞክራሲ ስርዓትን ከሚያራምዱ አገሮች በተለየና በአደገ መልኩ የግለሰብና የቡድን መብቶቻችንን አጣምሮ የሚያከብር የዴሞክራሲ አይነትን የሚፈቅድ ህገ-መንግስት ባለቤት ሆንን፡፡ በብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች የሚገለፀው የቡድን መብት ብቻ ሳይሆን የሃይማኖትና የፆታ እኩልነቶችም ሕገ-መንግስታዊ ዋስትና አግተዋቷል፡፡ ከኢኮኖሚ ልማት አኳያ የዜጎች አንጡራ ሀብት ጉልበት ማንም ሌላ ኃይል በማያዝበት ሁኔታ የዜጎች አንጡራ ሀብት ማለትም ሆነ፡፡ መሬት የጋራ የተፈጥሮ ፀጋ በመሆኑ በመንግስትና በህዝብ እጅ ሆኖ ዜጎች አልምተው ሊጠቀሙበት
6
ተደነገገ፡፡ ይህም የኢኮኖሚና የፖለቲካ ፍትሃዊነትን ያሰፈነ ውሳኔ ነው፡፡ በነዚህ ስኬታማ ተግባራት የያኔ ዘመን ታጋይ ወጣቶች ህዝባቸውን በማንቃትና በማደራጀት የመሪነት ድርሻቸውን ተወጥተዋል፡፡
በማህበራዊ ለልማት መስክ የፆታና የአካባቢ እንዲሁም የብሔር ልዩነቶች ሌሎች አድሎ የሚፈጥሩ ቅድመ ሁኔታዎች ሳይኖሩ ሁሉም እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ዜጎችን የመማር መብት የሚያስከብር ሆነ፡፡ የትምህርት ፍትሃዊነት በቦታ (በከተማና በገጠር) ተደራሽ መሆን ብቻ ሳይሆን በፆታ፣ በብሔርና ብሔረሰብ ፍትሃዊነቱ መረጋገጥ ያለበት መሆኑ በህገ-መንግስቱ በግልጽ ተመላክቷል፡፡ ከዴሞክራሲ ስርዓት አኳያ ስልጣን በህዝብ ይሁንታ እንጅ ከህዝብ ይሁንታ ውጭ ፈጽሞ የማይፈይድ መሆኑ በግልጽ ተመላከተ፡፡ ወጣቶች ሂደቱን በመምራትና ህዝቡን በማደራጀት ታሪካዊ ተልዕኳቸውን በብቃት ተወጥተዋል፡፡
በጥቅሉ መሰረታዊ የህዝብ መብቶችንና ጥቅሞችን በልማታዊና ዴሞክራሲያዊ አግባብ ለሚያረጋግጡ የህዝብ ጥያቄዎች በተሟላና ዘላቂነት ባለው መልኩ መልስ ሰጥቷል፡፡ የፌዴራሉን ህገ-መንግስት ተከትሎ የአማራ ክልልም የራሱን ህገ-መንግስት በምክር ቤቱ አፀደቀ፤ በክልሉ የሚገኙ ብሔረሰቦችም በሚኖሩበት መልክዓ ምድር የራሳቸውን ምክር ቤት አደራጅተው ራስን በራስ የማስተዳደር መብታቸውን ተጎናፀፉ፡፡ ለዘላቂ ሠላማችንና ለአብሮነታችን ዋስትናና ወሳኝ ቅድመ ሁኔታ የሆነው ህገ-መንግስት ፀድቆ ተግባራዊ መሆኑ፣ የኢትዮጵያን ልማታዊ ዴሞክራሲያዊ አብዮት ሁለተኛ ምዕራፍ ያበሰረ ትልቅ ድል ነው፡፡ በዚህ ረገድ የአማራ ክልል ወጣቶች ከአገራችን ወጣቶች ጋር ጣምራ ትግልና ድል ተጎናፅፈዋል፡፡
የአገራችን አብዮት ሦስተኛው ምዕራፍ በልማታዊ ዴሞክራሲያዊ ጎዳና፣ በህዝብ ይሁንታ ላይ የተመሰረተን ህዝባዊ መንግስት መስርቶና ዘላቂ ሠላምን አረጋግጦ፣ በመሰረተ ሰፊና በአደገ ገጽታ ስራ ላይ የዋለ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ፤ ፈጣን፣ ፍትሃዊ እንዲሁም ህዝቡ በየደረጃው ተጠቃሚ የሚሆንበትን የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማትን በቀጣይነት ማረጋገጥ ይጠይቃል፡፡
1.1.3 የህዝባዊ መንግስት ምስረታና የሠላም፣ ልማትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ውጤቶች
የኢትዮጵያ የመሰረታዊ ለውጥ ንቅናቄ ሦስተኛውና ረጅሙ ምዕራፍ ከ1988 ዓ.ም አንስቶ ቀጠለ፡፡ በዚህ ምዕራፍም የወጣቶች ግንባር ቀደም ንቅናቄ ሌላ መተኪያ አልነበረውም፡፡
ሀ/ አስተማማኝና ዘላቂ ሠላምን የማረጋገጥ ትግልና ውጤቶቹ
ድርጅታችን ብአዴን-ኢህአዴግና በሱ የሚመራው ልማታዊና ዴሞክራሲያዊ መንግስታችን ከሽግግር መንግስት ወቅት አንስቶ በትኩረት የያዘውን የሠላምና የመረጋጋት ተግባራት ቀጣይነት ለማስጠበቅ በትጋት ተንቀሳቅሷል፡፡ ለዘመናት ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ ህገ-ወጦችና፣ ጉልበተኞች የአቅመ ደካሞችን ሀብትና ንብረት እንዲሁም ህይወት እንደፈለጉ አደጋ ላይ እየጣሉ ያሻቸውን እያደረጉ የማይጠየቁበት፣ አልፎ አልፎም የሽፍትነትን ስራ በተከታታይ በማከናወናቸው በደጋፊዎቻቸው የሚሞካሹበት ነባራዊ ሁኔታ ነበር፡፡
ብአዴን-ኢህአዴግ ህዝቡን በማንቃት እና በማደራጀት ህገ-ወጥነትን ጉልበተኛነትን፣ በሌላው ላብና ጉልበት ተንጠልጥሎ የመኖርን መጥፎ አባዜ ለመግታት ከፍተኛ ጥረት አድርጓል፡፡ በአንድ በኩል ከደርግ ድምሰሳ ጋር ተያይዞ ተበትኖ የነበረውን በመቶ ሺዎች የሚቆጠር ወታደርና የጦር መሳሪያ በአግባቡ በመሰብሰብ ወታደሩን የሠላምና የተሃድሶ ትምህርት በመስጠትና በማስተማር ወደ ምርት ስራ እንዲገባ አቅም የፈቀደውን በማመቻቸት፣ የተበተነውን የጦር መሳሪያ በመልቀም ህዝባዊ ሚሊሻንና ፖሊስን አሰልጥኖ በማስታጠቁ ሠላማዊነትና ህጋዊነት እንዲረጋገጥ ከፍተኛ ጥረት አድርጓል፡፡ በዚህ ረገድ ወጣቶች ለህይወታቸው ሳይሰስቱ የህዝባቸውን አስተማማኝ ሰላምና ፀጥታ ለማስከበር ተንቀሳቅሰው በከፈሉት አኩሪ መስዋዕትነት የህዝባቸውን ሰላም አስተማማኝና ዘላቂ ማድረግ ችለዋል፡፡
ከመደበኛ የማምረት ተግባሩ ሳይነጠል የአካባቢውን ሠላም የሚጠበቅ ህዝባዊ ሚሊሻን በህዝብ ተሳትፎ በመመልመል እና በማሰልጠን እንዲሁም ቀጣይነት ያለው የአቅም ግንባታ በማድረግ ከህዝቡ የተደተራጀ እንቅስቃሴ ጋር በመሆን የሠላሙ ጉዞ በአስተማማኝ ሁኔታ እንዲዘልቅ ገንቢ ሚና ተጫውቷል፡፡ በፀረ-ዴሞክራሲ አምሳያ የተቀረፀውን የቀድሞ ፖሊስ የተሀድሶ ትምህርት ከመስጠት በተጨማሪ አዳዲስ የፖሊስ አባላት በህዝብ ተሳትፎ ተመልምለው፣ ህዝባዊ ሥነ-ምግባር የተላበሱ ሆነው ህዝብን እንዲያገለግሉ፣ የፖሊስ ኃይሉ ማዕከላዊ ስራ ወንጀል ከመፈፀሙ በፊት መከላከል እንዲሆን፣ ለዘላቂ ወንጀል መከላከል ሰፊ መሰረት ያለው ደግሞ ማህበረሰባዊ የፖሊስ እንቅስቃሴ (Community Pollicing) በዝርዝር የአፈፃጸም ስርዓት ተደራጅቶ ከከተማ እስከ ገጠር ህብረተሰቡ ከፖሊስ ጋር ተደራጅቶ ሰላምን አስተማማኝ የማድረግ ብቻ ሳይሆን ለዘላቂ ሠላም ቁልፍ ተፈላጊነት ያለው የአካባቢ ልማት እንዲረጋገጥ የበኩሉን አወንታዊ አስተዋጽኦ በማበርከት ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ ተግባር የወጣቶች ተሳትፎ ቀጥተኛና ተኪ ያልነበረው ነበር፡፡
ህዝባዊ ፖሊስና ሚሊሻ ከዋናው ባለቤት ከህዝቡ ጋር በመሆን በየደረጃው ከሚገኘው የአስተዳደር መዋቅር ቀጥተኛ አመራር እያገኘ ሠላም በራሱ ምርት እንዲሆን ዜጎች በነፃነት በፈለጉት ጊዜ፣ ከቦታ ቦታ ተዘዋውረው ኑሯቸውን ለማሻሻል እንዲተጉ፣ የሀብትና ንብረታቸው ከለላና ጠበቃ እንዲኖረው መሰረተ ሰፊና ቀጣይነት ያለው ስራ ተሰርቷል፡፡ ከወንጀል መከላከል አልፈው የሚፈፀሙ ወንጀሎችን አጣርቶ ለህግ በማቅረብ እና በማስቀጣት እንደ ሁሉም ተግባራቶቻችን ሁሉ የአፈፃጸም ድክመት ያለበት ቢሆንም ወሳኝ ገጽታው ወንጀለኞች ወንጀል ፈፅመው ከተጠያቂነት እንደማያመልጡ የሚያረጋግጡ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡ በአጠቃላይ ባለፉት 24 ዓመታት ሠላም በራሱና ከሌሎች የዴሞክራሲና የልማት ተግባራት ጋር በድምር ተመጋግበው እንዲያድጉ በዚሁ ሂደትም ህዝባችን የሠላም አየር እንዲተነፍስ፣ ሠላማዊና የሰከነ ሁኔታም እንዲረጋገጥ ብአዴንና ህዝቡ አኩሪ ተግባራትን ፈፅመዋል፡፡