Tuesday, 4 July 2017

የመፍትሔው አባት





አቶ መንግስቱ አስፋው ይባላሉ፡፡ በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ ዘጠኝ ነዋሪ ሲሆኑ የበርካታ አዳዲስ ፈጠራዎች ባለቤት ናቸው፡፡ ባለሙያው ውልደታቸውም ሆነ እድገታቸው እዚሁ አዲስ አበባ ሲሆን ገና ከልጅነታቸው አንስቶ ለፈጠራ ስራ ልዩ ፍላጎትና ተነሳሽነት ነበራቸው”” ችግር ፈቺ የፈጠራ ስራዎችን በወዳደቁ ቁሳቁስ አስመስሎ በመስራት የተለያዩ ሙከራዎችን ሲያደርጉ መቆየታቸውን ያስታውሳሉ፡፡ በዚህም በአካባቢው ህብረተሰብ ዘንድ አድናቆትን አትርፈው እንደነበር የሚገልፁት አቶ መንግስቱ ከ11ኛ ክፍል በኋላ ግን በወቅቱ የኢህአፓ አባል ሆነው በመቀላቀላቸው እንኳንስ የፈጠራ ስራ ሊሰሩ ይቅርና ወጥተው ለመግባትም ትልቅ ፈተና ሆኖባቸው ነበር፡፡

የመፍትሔው አባት






 አቶ መንግስቱ አስፋው ይባላሉ፡፡ በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ ዘጠኝ ነዋሪ ሲሆኑ የበርካታ አዳዲስ ፈጠራዎች ባለቤት ናቸው፡፡ ባለሙያው ውልደታቸውም ሆነ እድገታቸው እዚሁ አዲስ አበባ ሲሆን ገና ከልጅነታቸው አንስቶ ለፈጠራ ስራ ልዩ ፍላጎትና ተነሳሽነት ነበራቸው”” ችግር ፈቺ የፈጠራ ስራዎችን በወዳደቁ ቁሳቁስ አስመስሎ በመስራት የተለያዩ ሙከራዎችን ሲያደርጉ መቆየታቸውን ያስታውሳሉ፡፡ በዚህም በአካባቢው ህብረተሰብ ዘንድ አድናቆትን አትርፈው እንደነበር የሚገልፁት አቶ መንግስቱ ከ11ኛ ክፍል በኋላ ግን በወቅቱ የኢህአፓ አባል ሆነው በመቀላቀላቸው እንኳንስ የፈጠራ ስራ ሊሰሩ ይቅርና ወጥተው ለመግባትም ትልቅ ፈተና ሆኖባቸው ነበር፡፡

የደርግ ካድሬዎችም በተደጋጋሚ ጊዜ ማስጠንቀቂያና ከዛም ባለፈ ሊገድሏቸው ሲሉ ህይወታቸውን ለማትረፍ ቤተሰብ እንኳ ሳይሰናበቱ ትምህርታቸውን አቋርጠው ሽሽትን መረጡ፡፡ ከትውልድ ቀያቸውም ርቀው ከቀን ሰራተኛነት ጀምሮ በአናፂና ግንበኛነት እንዲሁም እስከ መንግስት ሰራተኛነት ያገኙትን ስራ በስጋትና በሰቆቃ በመስራት በነቀምት፣ በባህርዳር፣ በደጀንና ከዛም ወደ አሰብ በማቅናት አስቸጋሪ ህይወት አሳልፈዋል፡፡

Saturday, 1 July 2017

በከተማችን አማካይ የቀን ገቢ ግብር ትመና በ1996 ዓ.ም እንዲሁም በ2003 ዓ.ም ተሰርቷል፡፡ የግብር ትመናው ለዚህ ተብሎ በወጣው አዋጅ የተደገፈ ቢሆንም የአሰራር መመሪያ አልነበረውም፡፡ አሁን ላይ አዋጁ በአዲስ አዋጅ ከመተካቱ በተጨማሪ መመሪያ ቁጥር 123/2009 ተግባር ላይ ውሏል”” ከስድስት አመታት በኋላም አማካይ የቀን ገቢ ግብር ትመና ተከናውኗል፡፡ አጠቃላይ የአሰራር ሂደቶችንና የተካተቱ አዳዲስ መረጃዎችን በሚመለከት ከአዲስ አበባ ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ ከአቶ አትክልት ገ/እግዚአብሄር ጋር ከህዳሴ ጋዜጣ ያደረጉትን ቃለ ምልልስ እንደሚከተለው አቅርበናል፡፡




ህዳሴ፡- የቀን ገቢ ግብር ትመና ስራ በምን መልኩ ሲከናወን ቆየ?

አቶ አትክልት፡- አጠቃላይ ሂደቱ ከዝግጅት ምዕራፍ ጀምሮ ሰናየው ሊያሰራ የሚችል የማስፈፀሚያ ዕቅድ ታቅዷል፡፡ ከሚመለከታቸው ባለ ድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተደርጎበትም መተማመን ተፈጥሮበታል፡፡ በአሰራር መደገፍ ያለበትንም መመሪያ ቁጥር 123/2009 ተዘጋጅቷል”” ሌሎችም መረጃ ለመሰብሰብ የሚጠቅሙ ከቅፅ 001 እስከ ቅፅ 013 ያሉት የቀን ገቢ ትመና መረጃ መሰብሰቢያዎች ተዘጋጅተዋል፡፡ ሌላው አማካይ የቀን ገቢ ግምት የሚገምቱ አካላት ከየት ከየት ሴክተር መሆን አለባቸው የሚለውም በመመሪያው ጭምር ተመልሷል፡፡ አማካይ የቀን ገቢ መረጃ ሰብሳቢ ቡድን አራት አራት ሰው ሆኖ ተዋቅሯል፡፡ አማካይ የቀን ገቢ ግምት ምን ማለት ነው? በምን መልኩ መከናወን አለበት፣ አመላካቾቹ ምንድን ናቸው? በሚሉት እና በመሳሰሉት ለባለሙያዎቹ ዝርዝር ስልጠና ተሰጥቷል፡፡

ከዚህ ቡድን በተጨማሪ የኢንስፔክሽን ቡድንም ተቋቁሞ በሁሉም ወረዳዎች ስልጠና እንዲያገኝ ተደርጓል፡፡ የመረጃ አጣሪ ቡድንም አለ፡፡ ከዚህ ስልጠና በመቀጠልም ግብር ከፋዩንና የከተማችንን ነዋሪዎች እስከ ቀጠና ድረስ በየአደረጃጀቱ እንዲወያዩ ተደርጓል፡፡

በአጠቃላይ የዝግጅት ምዕራፉን በዝርዝር ገምግመናል፡፡ የተሳካ እንደነበርም አይተናል፡፡ ከዛም ከሚያዚያ 17 ጀምረን ወደ ትግበራ ምዕራፍ ገብተናል፡፡ አማካይ የቀን ገቢ ግምት በ1996 ዓ.ም ከተሰራ በኋላ በ2003 ዓ.ም ነው የተሰራው፡፡ በየሶስት አመቱ መሰራት ነበረበት”” ነገር ግን ባለፉት ስድስት ዓመታት አልሰራንም ነበር፡፡ ይህንን ታሳቢ በማድረግ አስፈላጊነቱን በማስፈፀሚያ እቅዳችን ጠቅሰናል፡፡ አንደኛው በየሶስት አመቱ መደረግ ነበረበት፤ በተለያዩ ምክንያቶች ስድስት ዓመት ቆይቷል፡፡ ሁለተኛው በአማካይ የቀን ገቢ ግምት ካለ ንግድ ፈቃድ የሚነግዱ በርካታ ነጋዴዎችን ወደ ስርዓቱ ለማስገባት፣ ሶሰተኛው ደግሞ የንግድ ፈቃድ ኑሯቸው ከዘርፋቸው ውጪ የሚነግዱም ስላሉ ከትርፉ እዳጌው ላይም መክፈል ከሚገባቸው አንፃር ልዩነት ስለ ሚኖር ይህንን ለማስተካከል ወደተግባር ተገብቷል፡፡

ሌላው ደግሞ የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅም ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ቀድሞ የነበረው የገቢ ግብር አዋጅ በአዋጅ ተሽሮ አዲስ አዋጅ ወጥቷል”” ይህ አዋጅ የደረጃ ለውጥ አድርጓል፡፡ ቀድሞ የነበረው አዋጅ እስከ 100 ሺህ ብር ዓመታዊ ሽያጭ ያለው ደረጃ ሐ ግብር ከፋይ ብሎ ነበር የሚያስቀምጠው፡፡ አሁን ግን እስከ 500 ሺህ ብር ተብሎ ተሻሽሏል፡፡ የበፊቱ አዋጅ የደረጃ ለ ግብር ከፋይ ከ100 ሺህ ብር በላይ ከ500 ሺህ ብር በታች ነበር፡፡ አሁን ግን ከ500 ሺህ ብር በላይ እስከ አንድ ሚሊዮን ብር ሆኗል፡፡ ደረጃ ሀ ከ500 ሺህ ብር በላይ ነበር በአዲሱ አዋጅ ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ ሆኗል፡፡ ስለዚህ ይህንን ታሳቢ ያደረገ የደረጃ ምደባ መደረግ የግድ ብሏል፡፡ ይህ የደረጃ ምደባም በ2003 ዓ.ም በነበረው መረጃ ሳይሆን አሁን በተጨባጭ ባለው መረጃ መሰረት ነው፡፡ ምክንያቱም ቢዝነስ በባህሪ ያድጋል ባለበት ይቆማል ወይም ደግሞ ወደ ኋላ ሊመለስ ስለሚችል እንደ አዲስ ታይቷል፡፡

ሌላው ደግሞ የገንዘብ የመግዛት አቅም ነው፡፡ በ2003 ዓ.ም የነበረው የገንዘብ የመግዛት አቅም አሁን ካለው የተለየ በመሆኑ እንደ አዲስ ስራው ተከናውናል፡፡ ለደረጃ ሐ የተሰበሰበውን መረጃ ወዲያውኑ እንጠቀምበታለን”” ምክንያቱም የቁርጥ ግብር ከፋዮች ናቸው፡፡ የሂሳብ መዝገብ የማቅረብ ግዴታ በህጉም አልተቀመጠም፡፡ አይገደዱም፡፡ የደረጃ ሀ እና የደረጃ ለ ግብር ከፋዮች ግን የሂሳብ መዝገብ የማቅረብ ግዴታ አለባቸው፡፡ ስለዚህ አማካይ የቀን ገቢ ግምት መረጃው ለደረጃ ሀ ና ለ የሂሳብ መዝገብ መረጃ ካላቀረቡ በዚሁ መረጃ የግብር አወሳሰን ስርዓቱ ይከናወናል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ ያቀረቡት የሂሳብ መዝገብ በባለስልጣኑ በህገ አግባብ ተቀባይነት ከአጣ እና አማካይ የቀን ገቢ ግብር ትመና መረጃ መጠቀም አስፈላጊ ነው ብሎ ተቋሙ ካመነ ይጠቀምበታለ፡፡ ሂደቱ ከዝግጅት ምዕራፍ ጀምሮ ትግበራ ምዕራፍን በዚህ መልኩ ማየት ይቻላል፡፡

ህዳሴ፡- አማካይ የቀን ገቢ ትመናው በየሶስት ዓመቱ መሆን ሲገባው የተራዘመበት ምክንያት ምንድን ነው?
አቶ አትክልት፡- የቀን ገቢ ግብር ትመናው በየሶስት ዓመቱ መሰራት ሲገባው ለ6 ዓመት የተራዘመው የከተማ አስተዳደሩ እና የተለያዩ ኮሚቴዎች በጋራ ተቀናጅተው የሚሰሩት ስራ በመሆኑ የተመቻቸ ጊዜ ስለሚያስፈልግ ነው፡፡ ሌላው ምክንያት ደግሞ አዲሱ የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅም ይጠበቅ ነበር፡፡ እንደሚወጣ ይታወቅ ስለነበረ ማለት ነው፡፡

ህዳሴ፡- እስከ አሁን ሲደረግ ከነበረው የቀን ገቢ ትመና የዘንድሮው በምን መልኩ ይለያል?

አቶ አትክልት፡- ከእስካሁኑ የቀን ገቢ ግብር ግምቶች ለየት የሚያደርገው ከአሰራር አንፃር ስንመለከት እራሱን የቻለ ሊመራ የሚችል መመሪያ አልነበረም፡፡ በ1996 ዓ.ም እና ለ2003 ዓ.ም ባደረግነው፡፡ አሁን ግን ራሱን የቻለ ይህን ሊመራ የሚችል መመሪያ ወጥቶለት ነው የተሰራው፡፡ መመሪያ ቁጥር 123/2009 ዝርዝር ነገሮችን ይዟል”” ሌላው ለየት የሚያደርገው ዘንድሮ የሰጠነው ስልጠና ዘርዘር ያለ ነው”” ሰፋ ያለ ጊዜም የተሰጠው ነው የባለሙያዎች ስልጠና ከኤንስፔክሽን ጋር ተያይዞ ባለፉት ጊዜያት በዚህ ደረጃ አልነበረም፡፡ አሁን ግን እንደየ ወረዳው ተጨባጭ ሁኔታ ስፋትና ጥብበት የኢንስፔክሽን ኮሚቴዎች ተቋቁመው ይህንን ስራ የመደገፍ የመከታተል ሰራ ሲሰሩ ነበር፡፡ ሌላው ደግሞ ከከተማ እስከ ወረዳ የተጠናከረ ቅንጅት ነበር፡፡ አስተዳደሩም እራሱ ገብቶበት በተለየ መልኩ ሲደግፍና ሲከታተል ነበር፡፡ በእነዚህ እና በመሳሰሉት ከባለፈው ለየት ይላል ብሎ መውሰድ ይቻላል፡፡

ህዳሴ፡- በከተማችን ምን ያህል ግብር ከፋይ ነጋዴ ይገኛል? ከፍተኛ፣ መካከለኛና ዝቅተኛ ብለው ቢገልፁልን?
አቶ አትክልት፡- በከተማችን ወደ 331 ሺህ ግብር ከፋዮች አሉ”” ከእነዚህ ውስጥ ግምት የማይገመትላቸ በመረጃ የሚስተናገዱ አሉ፡፡ አማካይ የቀን ገቢ ግምት መወሰድ አለበት ብለን የተንቀሳቀስንባቸው እስከ 200 ሺህ ይደርሳሉ፡፡ ከእነዚህ ውስጥ 68 በመቶው የደረጃ ሐ ግብር ከፋዮች ናቸው፡፡ 21 በመቶው ደግሞ ደረጃ ሀ ሲሆን ሌላው 11 በመቶ የሚሆነው የደረጃ ለ ግብር ከፋይ ነው፡፡ የእስካሁኑ መረጃ የሚያሳየው፡፡ የአሁኑ ግን ገና እየተሰራ ነው፤ ወደፊት እንገልፃለን፡፡

ህዳሴ፡- የቀን ገቢ ግምት የማይሰራላቸው የትኞቹ ዘርፎች ናቸው?

አቶ አትክልት፡- የማይገመትላቸው ግብር ከፋዮች በግልፅ በስልጠና ማንዋላችን ላይም ተቀምጠዋል፡፡ ለምሳሌ መረጃ የሚገኝባቸው አስመጭና ላኪ ከሆኑ አንገምትም፡፡ ምክንያቱም ሲያስመጣና ሲልክ መረጃ እናገኛለን”” ስራ ተቋራጮ ውል አላቸው፣ የኮንስትራክሽን መሳሪያ ኪራይ፣ መኪና ማከራየት፣ አማካሪነት፣ አስጎብኝና የጉዞ ወኪል፣ የውጪ አገር ስራና አሰሪ አገናኞች፣ ትራንስፖርትም የቁርጥ ግብር ከፋይ ነው፡፡ ይህን ያህል መጫን የሚችል መኪና ይህን ያህል ይከፍላል ተብሎ ተለይቷል”” ወፍጮ ቤቶችም ይህን ያህል ቋት ያለው ይህን ያህል ይከፍላል ተብሎ ተቀምጧል፡፡ በመሆኑም አማካይ የቀን ገቢ ግብር ትመና መረጃ መሰብሰብ የሚያስፈልገው ከነዚህ መሰል ዘርፎች ውጪ ለተመሰማሩ ነጋዴዎች ነው፡፡

ህዳሴ፡- በግብር ትመና ስራው ያጋጠሙ ችግሮችስ ምን ምን ናቸው? እንዴትስ ተፈቱ?

አቶ አትክልት፡- በአማካይ የቀን ገቢ ግምት መረጃ አሰባሰብ ያጋጠሙ ችግሮች በራሳችን ላይ በነበሩ ክፍተቶች አንደኛው በቀን በአንድ ቡድን ከ20 እስከ 25 ለሚሆኑት ነጋዴዎች አማካኝ የቀን ገቢ ግምት እንሰራለን ብለን ነበር ነገር ግን ከ7 እስከ 10 ነው አፈፃፀማችን”” በአንድ ወር ውስጥ እናጠናቅቃለን ባልነው መሰረት ለመጓዝ አዳጋች ነበር፡፡ ሁለተኛው ችግር በአማካይ የቀን ገቢ ግምት ሰብሳቢው ቡድን የሚሞሉ ቅፆችን በአግባቡ ያለመሙላት ችግር ይታይ ነበር፡፡ ወደ መረጃ ቋትም በየእለቱ እንዲገባ መመሪያው ያዝዝ ነበር፡፡ ማንጠባጠቦች ነበሩ፡፡ የኢንስፔክሽን ቡድኑ የድጋፍና ክትትል አግባብም በጠንካራ ዲሲፕሊን እንዲመራ ካስቀመጥነው አንፃር የተወሰነ ክፍተት ታይቷል፡፡ ገምግመን የማስተካከያ እርምጃ ወስደናል፡፡ ሌላኛው በግብር ከፋዩ ህብረተሰብ ያጋጠመን ችግር ነው”” ለሽያጭ የተዘጋጁ እቃዎችን መሰወር፣ ሱቆችን ማሳነስ፣ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ትክክለኛ መረጃ እንዳያገኝ የተለያዩ እንቅፋቶችን መፍጠር፣ ህፃናትን ማስቀመጥ፣ ቋንቋውን የማይናገሩ ልጆችን ማስቀመጥ፣ ሱቅ ዘግቶ መጥፋት የመሳሰሉት ተስተውለዋል፡፡

የግብር ከፋዮች አደረጃጀቶችም ስለነበሩ ከነሱ ጋር በመነጋገር ችግሩ ትርጉም ባለው መልኩ እንዲፈታ አድርገናል፡፡ የተወሰኑ ግለሰቦች ግን ተደጋጋሚ ስላስቸገሩ አማካኝ የቀን ገቢ መረጃውን ቀደም ብለንም አይተን ስለነበር በዚያ መሰረት ሰርተናል፡፡ ግብር ከፋዩ ቅሬታ ካለበት በህግና ስርዓቱ መሰረት አቅርበው የማታይ ይሆናል፡፡ አማካይ የቀን ገቢ ግብር መረጃ መሰብሰብ የጀመርነው ሚያዚያ 17 ነው፡፡ ነገር ግን ቡድኖቹ ቀደም ብለው የሚገምቱት ብሎክ ተሰጥቷቸው የአካል ምልከታ ለሁለት ቀን ያህል ስለ አደረጉ ቢዝነሳቸው ምን ይመስላል የሚለውን ቀድመው መረጃ ወስደዋል፡፡ ይህንን መረጃ መሰረት አድርገው ሰርተውታል፡፡
ህዳሴ፡- ግብር በሚተምኑ ባለሙያዎች በኩል የነበረው የኪራይ ሰብሳቢነት አስተሳሰብና ተግባርስ እንዴት ይገለፃል?
አቶ አትክልት፡- እንደዚህ አይነት ችግሮች አጋጥመዋል፤ በተወሰነ መልኩም ቢሆን፡፡ ‘እኔ ነኝ የምገምተው እንደዚህ አዋጡልን’ የሚሉና መሰል ችግሮች ነበሩ፡፡ ግብር ከፋዮች ወዲያውኑ ለባለ ስልጣን መስሪያ ቤቱ ጥቆማ አድርሰዋል፡፡ ችግር እንዳለባቸው የተጠቆሙትን ከቡድኑ እንዲወጡ የማድረግ ስራ ወዲያውኑ ሰርተናል፡፡ ከዚያም በተቋሙ አሰራ ርመሰረት እንዲጠየቁ እየተደረገ ነው፡፡ መረጃው እየተጣራ ማለት ነው”” መመሪያውም በዚህ አግባብ ስላስቀመጠ፡፡

ህዳሴ፡- የኪራይ ሰብሳቢነት አስተሳሰብና ተግባርን ለመከላከል ተቋሙ ምን አይነት አሰራር ዘርግቶ ተንቀሳቅሷል?

አቶ አትክልት፡- አሰራሩ በመመሪያ ቁጥር 123/2009 በግልፅ ተቀምጧል፡፡ ፀብ፣ ዝምድና ካለ ወዲያውኑ አሳውቆ ከኮሚቴው አባልነት የመውጣትና በሌላ አካል እንዲገመት የመጠየቅ መብት ለፈፃሚውም ለግብር ከፋዩም ተመላክቷል፡፡ ግብር ከፋዩም እከሌ ከኔ ጋር ዝምድና አለው ወይም ፀብ አለው ስለዚህ መገመት አይችልም የማለት መብት አለው፡፡
ከዚህ አሰራር ከተላለፈ ደግሞ የሰራተኛ አስተዳደር ህግ አለ፡፡ በዚያ አግባብ የሚጠየቅበት ግልፅ አሰራር ተዘርግቶ ወይይት ተደርጎበት
እናአምኖበት ነው የገባው፡፡ በተግባር ደግሞ ቅድመ እንዳልኩት ኪራይ ለመሰብሰብ ጥረት ያደረጉ አካላት ነበሩ፡፡ ከቡድኑ የማውጣትና በህግ አግባብ ተጠያቂ የማድረግ ስራ እየተከናወነ ነው፡፡ ስለዚህ ለኪራይ ሰብሳቢነት አስተሳሰብና ተግባር ተገቢው እርምጃ ቀደም ብሎ በአሰራር መመሪያው ተገልጿል፡፡ ቅፆችን ግልፅ የማድረግ ስራም ጭምር ተሰርቷል፡፡ ቅፅ 001 የሚባለውን ወዲያውኑ ለግብር ከፋዩ እንዲሰጠው ተደርጓል፡፡

ህዳሴ፡- የቀን ገቢ ግብር ትመናው በተያዘለት የጊዜ ገደብ ተጠናቅቋል ማለት ይቻላል?

አቶ አትክልት፡- ሚያዚያ 17 ነው ስራው የተጀመረው፡፡ በ30 ቀን ውስጥ የመጨረስ እቅድ ነበርን፡፡ ማስተካከያ ስንሰራ የተወሰነ ቀን አቋርጠናል፡፡ በ30 ቀናችን አጠናቅቀናል፡፡ በእቅዳችን መሰረት በተያዘለት የጊዜ ገደብ አጠናቅቀናል፡፡
ህዳሴ፡- የቀን ገቢ ትመናውን ህጋዊና ፍትሀዊ ነው ማለት የሚያስችሉ አሰራሮችን በጥብቅ የመከተሉ ጉዳይ እንዴት ተከናወነ?
አቶ አትክልት፡- የቀን ገቢ ግምት ይህን ያህል ያገኛል ብለን በማየት ብቻ ሳይሆን በተለያዩ አመላካቾች በመታገዝ ነው የሚሰራው፡፡ ለምሳሌ ፀጉር ቤት ስንት ወንበር አለው የሚለው ለገቢው አመላካች ነው፡፡ ሌሎች የጥፍር ቀለምና መሰል ቁሳቁሶችን ጎን ለጎን የሚሸጥ ከሆነም ሌላው አመላካች ነው፡፡ ግምት ስለሆነ በተወሰነ መልኩ ችግር አይኖርም ብሎ መውሰድ ባይቻልም እንዳይጎሉ ግን በጥንቃቄ ተንቀሳቅሰናል፡፡ የግል ማስታወሻ በማየት፣ የሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያ በማየት፣ የአካባቢውን ገበያ (መጀመሪያ መንገድ፣ ሁለተኛ መንገድ፣ መጋቢ መንገድ፣ ሶስተኛ መንገድ) በተመሳሳይ አመላካቾች ናቸው፡፡ በመሆኑም በተቻለ መጠን ፍትሃዊ እንዲሆን ተንቀሳቅሰናል፡፡

ህዳሴ፡- አጎራባች ቀጠናዎች በተቀናጀ መልኩ ትመናውን እንዲያስኬዱ ማድረጉስ ምን ይመስላል?
አቶ አትክልት፡- በመመሪያችንም በግልፅ ተቀምጧል፡፡ በተለይ አዋሳኞች አሉ ክፍለ ከተማ ከክፍለ ከተማ ወረዳ ከወረዳ አንዱ መንገድ ከአንዱ መንገድ የሚዋሰኑ አሉ፡፡ ይሄ ጉራማይሌ እንዳይሆን ኮሚቴዎቹ እየተነጋገሩ በጋራ እንዲሰሩ ነው የተደረገው፡፡ ለምሳሌ ቦሌንና የካን የሚሰሩ በአዋሳኝ ቦታዎች ላይ ኮሚቴዎቹ ተናብበው እንዲሰሩ ተደርጓል”” ሌላው ከከተማ እስከ ወረዳ በየጊዜው መረጃው እየተገመገመ በቅንጅት ነው የተሰራው፡፡

ህዳሴ፡- ከዚህ በኋላ የተቋሙ የቀጣይ አቅጣጫ ምንድን ነው?

አቶ አትክልት፡- አማካኝ የቀን ገቢ ግምቱ ለግብር ከፋዩ በደብዳቤ እንዲደርሰው ይደረጋል፡፡ ቅሬታም ካለ ቅሬታውን ያቀርባል፡፡ ይህንን የሚቀበል በየወረዳው የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ ተደራጅቷል፡፡ በየክፍለ ከተማውም በተመሳሳይ ተዋቅሯል፡፡
ከዚህ በኋላ ወደ ግብር እና ታክስ ወደ መክፈል ይገባል፡፡ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ እስከ ጥቅምት 30 የግብርና የታክስ መክፈያ ወቅት ነው፡፡ ከሀምሌ 1 እስከ 30 ደረጃ ሐ ግብርና ታክስ ይከፍላል፡፡ ደረጃ ለ ከሀምሌ 1 እስከ ጳጉሜ መጨረሻ ገብርና ታክሰ ይከፍላል፡፡ ደረጃ ሀ ደግሞ ከሀምሌ 1 እስከ ጥቅምት 30 ግብር እና ታክሱን ይከፍላል፡፡

ህዳሴ፡- በመጨረሻም ለግብር ከፋዩ ህብረተሰብ የሚያስተላልፉት መልዕክት ካለ?

አቶ አትክልት፡- አማካኝ የቀን ገቢ ግብር ግምት መረጃ ሲሰበሰብ በርካታ ግብር ከፋዮቻችን ስራው የተቃና እንዲሆን ከኮሚቴውና ከባለስልጣኑ ጎን ሆነው ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና እናቀርባለን፡፡ መረጃ በመሰወር እና ስራው እንዲደናቀፍ ሲንቀሳቀሱ የነበሩት ደግሞ ግብርን የመክፈልን ሀገራዊ ዓላማ ተረድተው ግዴታቸውን ወደፊትም በአግባቡ እንዲወጡ መልዕክት አስተላልፋለሁ፡፡ ግብር ከፋዮቻችን በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ግብርና ታክሳቸውን እንዲከፍሉ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ፡፡

ህዳሴ፡- ስለነበረን ቆይታ እናመሰግናለን፡፡
አቶ አትክልት፡- እኔም አመሰግናለሁ፡፡

Tuesday, 27 June 2017

የኦሮሚያ ክልል በአዲስ አበባ ከተማ ላይ ያለውን ህገ-መንግሥታዊ ልዩ ጥቅም አስመልክቶ የቀረበ መግለጫ

 

የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ሰፊ ውይይት ካካሄዱበት በኋላ በተወካዮቻቸው አማካይነት ያፀደቁት ህገ-መንግሥት የሁሉንም ሕዝቦች መብቶችና ጥቅምች የሚያስጠብቅ ነው፡፡

ህገ-መንግሥቱም የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የቃል-ኪዳን ሰነድ ሲሆን ዓላማውም በሕዝቦች መፈቃቀድና ፍላጎት እንዲሁም ዴሞክራሲያዊ አንድነት ለማጎልበት እንዲቻል በጋራ ያፈሯቸው እሴቶችና ሃብቶች እንዲሁም ትስስሮች እንዳሏቸው በማመን- በታሪካቸው ሂደት ውስጥ ያጎለበቷቸውን የጋራ ጉዳዮች ይበልጥ ለማበልፀግና የተዛቡ ግንኙነቶችንም በማረም አንድ ጠንካራ የጋራ ኢኮኖሚያዊ ማህበረሰብ እና የጋራ ፖለቲካዊ ማህበረሰብ ለመገንባትና ለማጠናከር የታለመ ነው፡፡

Tuesday, 13 June 2017

በሳዑዲ በኢትዮጵያውያኑ ላይ የትናንቱ እንዳይደገም



 

 

በአረብ ሀገራት ኢትዮጵያውያን በብዛት ከሚኖሩባቸው ሀገራት አንዷ ሳዑዲ አረቢያ ናት።

 በሀገሪቱ በየአመቱ የሚካሄዱ ሃይማኖታዊ ስነስርአቶችን ጨምሮ በልዩ ልዩ መንገዶች ወደ ሀገሪቱ የሚገቡ ዜጎች በህጋዊም ሆነ የሀገሪቱን ህግ ተላልፈው ለአመታት ሲኖሩባት የቆችው ይህቺ ሀገር፥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በውጭ ሀገራት ዜጎች ዙሪያ ጠንካራ ህጎችን በማውጣት እርምጃ እየወሰደች የምትገኝ ሀገር ሆናለች። እንደ ሌሎች ሀገራት የውጭ ዜጎች በልዩ ልዩ የስደት ሰበቦች በሀገሪቱ ለመኖር ቢፈልጉ ይህንን የሚያስተናግድ ህግ የላትም። በአብዛኛው ከተለያዩ ሀገራት ወደ ሀገሪቱ የገቡ የውጭ ዜጎች ይኖሩባታል።

ኢኮኖሚዋ ከነዳጅ በሚገኝ ገቢ ላይ የተመሰረተው ይህች አገር የምርቱ በዓለም ገበያ ላይ ዋጋው እየወረደ መምጣት ፈተና ሆኖባታል። ይህንን ተፅእኖ ለመቋቋም የመንግስት የወጪ ቅነሳን የሚያበረታቱ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን አዘጋጅታ በመተግበር ላይ የምትገኝ ሲሆን፥ ስራ አጥ ለሆኑ የአገሬው ሰዎች የስራ እድልን ያመጣሉ ያለቻቸውን እርምጃዎችንም ስትወስድ ቆይታለች። ከእነዚህ እርምጃዎች መካከል በተለይም በአገልግሎት ዘርፎች ላይ የሚገኙ ስራዎች ያለ አግባብ በውጭ አገራት ዜጎች ተይዘዋልና እነዚህን የስራ እድሎች ለሳዑዲ ዜጎች ክፍት ሊደረጉ ይገባል ይላሉ ፖለቲከኞቿ። ይህ እንዲሆን ህጋዊ ሰነድ የሌላቸውን የተለያዩ አገራት ዜጎች ከግዛቷ ማስወጣትን እንደ አንድ አማራጭ በመያዝ በተለያዩ ጊዜ በዘመቻ ስታስወጣ ቆይታለች።

Wednesday, 24 May 2017

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ-መንግስት መሰረታዊ ዓላማዎች

የኢ... ሕገ-መንግስት የኢትዮጵያ ህዝቦች በሃገራቸው መፃኢ ዕድል ላይ ብሩህ ተስፋ ሰንቀው እንደ አንድ ማህበረሰብ እንዲነሳሱ የሚያደርጋቸውን ዓላማ ያስቀመጠ ነው፡፡ ዓላማዎቹ በህገ-መንግስቱ መግቢያ ላይ የሰፈሩ ናቸው፡ ይህም አጠር ባለ መንገድ ሲገለፅ ያለፈውን የተዛባ ግንኙነት በማስተካከል እና ባለፈው ያፈሩትን የጋራ ሃብት፣ ትስስርና እሴት ስላላቸው በፍላጎታቸውና በራሳቸው ፈቃድ ዘላቂ ሰላም፣ ዋስትና ያለው ዴሞክራሲ እንዲሰፍን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገታቸው እንዲፋጠን የሚያስችል የጋራ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ማህበረሰብ ለመገንባት ቃል የገቡ መሆናቸውን፣ ይህን ለማሳካት የግለሰብም ሆነ የብሄሮች ብሄረሰቦች ህዝቦች መብቶችና የፆታ እኩልነት ማረጋገጥ፣ ባህሎችና ሃይማኖቶች ያለ አድሎና ልዩነት እንዲራመዱ ማድረግ ፅኑ እምነታቸው እንደሆነ መወሰናቸውን …. የሚል ነው፡፡ የሕገ-መንግስታችን መግቢያ ዘላቂ ሰላም፣ ዋስትና ያለው ዴሞክራሲ፣ ፈጣን ኢኮኖሚያዊ ልማት፣ አንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ግንባታ የሚሉ ዓላማዎችና ራዕዮች በግልፅ አስቀምጧል፡፡ እነዚህ የህገ-መንግስታችን ዓላማዎች የማይነጣጠሉና እርስ በርሳቸው የተሳሰሩ ናቸው፡፡

Tuesday, 1 November 2016

‹‹ እየታደስን እንሰራለን እየሰራን እንታደሳለን›› ነው





1.ግሮቻችንን ያለምህረት እንገምግም፣ ከችግሮቻችን እንቆራረጥ

2009 በድርጅታችን ኢህአዴግ ሰፊ ዳግም በጥልቀት መታደስ ንቅናቄ የሚካሄድበት መሆኑ ይታወቃል፡፡ በጥልቀት መታደስ ለምን አስፈለጊ ሆኖ እንደተገኘም በቂ የህዝብ ግንኙነት ስራ ተሰርቷል ማለት ይቻላል፡፡ መዋቅራችን ብቻ ሳይሆን በጥልቀት መታደስ ለምን አስፈለገ በሚለው ዙሪያ በህዝብ ኮንፈረንስም መግባበት ለመፍጠር ጥረት ተደርጓል፡፡ አሁን በምንገኝበት ድርጅታዊና ሃገራዊ ሁኔታ ጉዟችንን ሊቀለብሱ የሚችሉ ፖለቲካዊ ብልሽቶች አጋጥመውናል፡፡ ይህንን ሲባል ግን ግምገማው እስካሁን ለመጣነው ጉዞና ለተገኙ ድሎች በዜሮ የሚያጣፋ መሆን የለበትም፡፡
ነባራዊ ሁኔታው ስንገመግም መነሻችን እና አተያየታችን የተዛባ መሆን የለበትም፡፡ ያጋጠሙን የውስጥ ድርጅትና ሀገራዊ ተግዳሮቶችና እንቅፋቶች በስኬቶች ላይ ሆነን ያጋጠሙን ናቸው የሚለውን የድርጅታችን ግምገማ በጥብቅ መጨበጥ ይገባል፡፡ በመሆኑም በጥልቀት መታደስ አለብን ሲባል ከችግሮቻችን መቆራረጥ አለብን ማለት እንጂ እስካሁን ያሳካናቸው ስራዎቻችንን የሚደፈጥጥና የሚክድ መሆን አለበት ማለት አይደለም፡፡ በጥልቀት መታደስ አስፈላጊ የሆነው እሰካሁን የረባ ስራ ስላልሰራን ይህንን ሀጥያት ለመናዘዝ ሳይሆን በስኬት ላይ ሆነን ያጋጠሙን ችግሮች ግን አቃልሎ መታየት የሌለባቸው ብቻ ሳይሆኑ በተለየ የተሃድሶ ንቅናቄ መልክ በፍጥነት ካልቀለበስናቸው አጠቃላይ ድሎቻችንም የሚበሉ የህዳሴ ጉዟችንም የሚያደናቅፉ ከባድ ችግሮች  ናቸው፡፡ የመጀመሪያው ሊሰመርበት የሚገባና መግባበት ሊደረስበት የሚገባ ነጥብ ይህ ነው፡፡

Wednesday, 24 August 2016

ከቀለም አብዮት በስተጀርባ (behind the color revolution) የተደበቁ ቁማርተኞች





I. የቀለም አብዮት (color revolution) መነሻ ምክንያቶች

እንደ አውሮፓ አቆጣጠር በ1991 ዓ ም የተባበሩት የራሽያ ሶሺያሊስት ሪፓብሊክ ሀገራት ሲበታተኑ ከከረረ የአይዲዮሎጂ ልዩነት ጋር በዓለም ሁለት ኃያላን ሀገራት ተፈጠሩ። እነዚህ ኃያላን የሩሲያ የልማታዊ መንግሥት አስተሳሰብ ጎራና የአሜሪካ የገብያ አክራሪ አራማጅ ኃያላን ጎራዎች ናቸው። ሁለቱ ጎራዎች ሌሎች ሀገራትን በተጽዕኗቸው ሥር ለማስገባት የሚያደርጉት ጥረትና ድካም እንደ ተጠበቀ ሆኖ የአሜሪካና የምዕራብ አውሮፓ ኃያላን ዓለምን በሙሉ በአንድ የገብያ አክራሪነት ካምፕ ውስጥ ለማስገባት በተለያዩ ዘዴዎች አንዱን ከሌላው እያጋጩ በማተራመስ ዘዴ ሠርገው ለመግባትና የኃሳብ የበላይነታቸውን ለመጫን ብዙ ሞክረዋል፣ እስከ ዛሬም ቀጥለዋል።
በሌላ በኩል የመንግሥታዊ ካፒታሊዝም ባህሪን ይዞ የቀጠለውና በኋላም በዲንግ ምፒንግ ጠንካራ አመራር እየዳበረ የመጣው የቻይና ልዩ ፖለቲካል ኢኮኖሚ የገብያ አክራሪ አስተሳሰብን እንደ ወረደ ሳይቀበል በራሱ ተጨባጭና ነባራዊ ሁኔታ አስተካክሎ በመቀጠሉ ተአምራዊ በሆነ ፍጥነት እያንሠራራ ቀጠለ። በሩሲያም በኩል በተለይ በብላድሚር ፑቲን አመራር የራሱን ተጨባጭ አቅም መሠረት ያደረገ ልማታዊ ባህሪን አጠናክሮ በመቀጠሉ አሁንም ዓለም በአንድ የፖለቲካል ኢኮኖሚ ዋልታ ልትመራ እንደማትችል የሚያሳይ ክስተት እያቆጠቆጠ መጣ። ያልተጠበቁ እና የተለያዩ ባህርያት ያሏቸው የኢኮኖሚ ዋልታዎች የመሥፋፋት ክስተት በሌሎችም የምሥራቅ እስያ ሀገራት እያንሠራራ መምጣቱን ተከትሎ ሌሎች ሀገራት ወደእነዚህ አዳዲስ ዋልታዎች ጎራ እንዳይቀላቀሉ የቀለም አብዮት አጀንዳን መጋበዝ ጀመሩ።