Tuesday, 4 July 2017

የመፍትሔው አባት





አቶ መንግስቱ አስፋው ይባላሉ፡፡ በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ ዘጠኝ ነዋሪ ሲሆኑ የበርካታ አዳዲስ ፈጠራዎች ባለቤት ናቸው፡፡ ባለሙያው ውልደታቸውም ሆነ እድገታቸው እዚሁ አዲስ አበባ ሲሆን ገና ከልጅነታቸው አንስቶ ለፈጠራ ስራ ልዩ ፍላጎትና ተነሳሽነት ነበራቸው”” ችግር ፈቺ የፈጠራ ስራዎችን በወዳደቁ ቁሳቁስ አስመስሎ በመስራት የተለያዩ ሙከራዎችን ሲያደርጉ መቆየታቸውን ያስታውሳሉ፡፡ በዚህም በአካባቢው ህብረተሰብ ዘንድ አድናቆትን አትርፈው እንደነበር የሚገልፁት አቶ መንግስቱ ከ11ኛ ክፍል በኋላ ግን በወቅቱ የኢህአፓ አባል ሆነው በመቀላቀላቸው እንኳንስ የፈጠራ ስራ ሊሰሩ ይቅርና ወጥተው ለመግባትም ትልቅ ፈተና ሆኖባቸው ነበር፡፡

የመፍትሔው አባት






 አቶ መንግስቱ አስፋው ይባላሉ፡፡ በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ ዘጠኝ ነዋሪ ሲሆኑ የበርካታ አዳዲስ ፈጠራዎች ባለቤት ናቸው፡፡ ባለሙያው ውልደታቸውም ሆነ እድገታቸው እዚሁ አዲስ አበባ ሲሆን ገና ከልጅነታቸው አንስቶ ለፈጠራ ስራ ልዩ ፍላጎትና ተነሳሽነት ነበራቸው”” ችግር ፈቺ የፈጠራ ስራዎችን በወዳደቁ ቁሳቁስ አስመስሎ በመስራት የተለያዩ ሙከራዎችን ሲያደርጉ መቆየታቸውን ያስታውሳሉ፡፡ በዚህም በአካባቢው ህብረተሰብ ዘንድ አድናቆትን አትርፈው እንደነበር የሚገልፁት አቶ መንግስቱ ከ11ኛ ክፍል በኋላ ግን በወቅቱ የኢህአፓ አባል ሆነው በመቀላቀላቸው እንኳንስ የፈጠራ ስራ ሊሰሩ ይቅርና ወጥተው ለመግባትም ትልቅ ፈተና ሆኖባቸው ነበር፡፡

የደርግ ካድሬዎችም በተደጋጋሚ ጊዜ ማስጠንቀቂያና ከዛም ባለፈ ሊገድሏቸው ሲሉ ህይወታቸውን ለማትረፍ ቤተሰብ እንኳ ሳይሰናበቱ ትምህርታቸውን አቋርጠው ሽሽትን መረጡ፡፡ ከትውልድ ቀያቸውም ርቀው ከቀን ሰራተኛነት ጀምሮ በአናፂና ግንበኛነት እንዲሁም እስከ መንግስት ሰራተኛነት ያገኙትን ስራ በስጋትና በሰቆቃ በመስራት በነቀምት፣ በባህርዳር፣ በደጀንና ከዛም ወደ አሰብ በማቅናት አስቸጋሪ ህይወት አሳልፈዋል፡፡

Saturday, 1 July 2017

በከተማችን አማካይ የቀን ገቢ ግብር ትመና በ1996 ዓ.ም እንዲሁም በ2003 ዓ.ም ተሰርቷል፡፡ የግብር ትመናው ለዚህ ተብሎ በወጣው አዋጅ የተደገፈ ቢሆንም የአሰራር መመሪያ አልነበረውም፡፡ አሁን ላይ አዋጁ በአዲስ አዋጅ ከመተካቱ በተጨማሪ መመሪያ ቁጥር 123/2009 ተግባር ላይ ውሏል”” ከስድስት አመታት በኋላም አማካይ የቀን ገቢ ግብር ትመና ተከናውኗል፡፡ አጠቃላይ የአሰራር ሂደቶችንና የተካተቱ አዳዲስ መረጃዎችን በሚመለከት ከአዲስ አበባ ከፍተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ ከአቶ አትክልት ገ/እግዚአብሄር ጋር ከህዳሴ ጋዜጣ ያደረጉትን ቃለ ምልልስ እንደሚከተለው አቅርበናል፡፡




ህዳሴ፡- የቀን ገቢ ግብር ትመና ስራ በምን መልኩ ሲከናወን ቆየ?

አቶ አትክልት፡- አጠቃላይ ሂደቱ ከዝግጅት ምዕራፍ ጀምሮ ሰናየው ሊያሰራ የሚችል የማስፈፀሚያ ዕቅድ ታቅዷል፡፡ ከሚመለከታቸው ባለ ድርሻ አካላት ጋር ውይይት ተደርጎበትም መተማመን ተፈጥሮበታል፡፡ በአሰራር መደገፍ ያለበትንም መመሪያ ቁጥር 123/2009 ተዘጋጅቷል”” ሌሎችም መረጃ ለመሰብሰብ የሚጠቅሙ ከቅፅ 001 እስከ ቅፅ 013 ያሉት የቀን ገቢ ትመና መረጃ መሰብሰቢያዎች ተዘጋጅተዋል፡፡ ሌላው አማካይ የቀን ገቢ ግምት የሚገምቱ አካላት ከየት ከየት ሴክተር መሆን አለባቸው የሚለውም በመመሪያው ጭምር ተመልሷል፡፡ አማካይ የቀን ገቢ መረጃ ሰብሳቢ ቡድን አራት አራት ሰው ሆኖ ተዋቅሯል፡፡ አማካይ የቀን ገቢ ግምት ምን ማለት ነው? በምን መልኩ መከናወን አለበት፣ አመላካቾቹ ምንድን ናቸው? በሚሉት እና በመሳሰሉት ለባለሙያዎቹ ዝርዝር ስልጠና ተሰጥቷል፡፡

ከዚህ ቡድን በተጨማሪ የኢንስፔክሽን ቡድንም ተቋቁሞ በሁሉም ወረዳዎች ስልጠና እንዲያገኝ ተደርጓል፡፡ የመረጃ አጣሪ ቡድንም አለ፡፡ ከዚህ ስልጠና በመቀጠልም ግብር ከፋዩንና የከተማችንን ነዋሪዎች እስከ ቀጠና ድረስ በየአደረጃጀቱ እንዲወያዩ ተደርጓል፡፡

በአጠቃላይ የዝግጅት ምዕራፉን በዝርዝር ገምግመናል፡፡ የተሳካ እንደነበርም አይተናል፡፡ ከዛም ከሚያዚያ 17 ጀምረን ወደ ትግበራ ምዕራፍ ገብተናል፡፡ አማካይ የቀን ገቢ ግምት በ1996 ዓ.ም ከተሰራ በኋላ በ2003 ዓ.ም ነው የተሰራው፡፡ በየሶስት አመቱ መሰራት ነበረበት”” ነገር ግን ባለፉት ስድስት ዓመታት አልሰራንም ነበር፡፡ ይህንን ታሳቢ በማድረግ አስፈላጊነቱን በማስፈፀሚያ እቅዳችን ጠቅሰናል፡፡ አንደኛው በየሶስት አመቱ መደረግ ነበረበት፤ በተለያዩ ምክንያቶች ስድስት ዓመት ቆይቷል፡፡ ሁለተኛው በአማካይ የቀን ገቢ ግምት ካለ ንግድ ፈቃድ የሚነግዱ በርካታ ነጋዴዎችን ወደ ስርዓቱ ለማስገባት፣ ሶሰተኛው ደግሞ የንግድ ፈቃድ ኑሯቸው ከዘርፋቸው ውጪ የሚነግዱም ስላሉ ከትርፉ እዳጌው ላይም መክፈል ከሚገባቸው አንፃር ልዩነት ስለ ሚኖር ይህንን ለማስተካከል ወደተግባር ተገብቷል፡፡

ሌላው ደግሞ የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅም ማሻሻያ ተደርጎበታል፡፡ ቀድሞ የነበረው የገቢ ግብር አዋጅ በአዋጅ ተሽሮ አዲስ አዋጅ ወጥቷል”” ይህ አዋጅ የደረጃ ለውጥ አድርጓል፡፡ ቀድሞ የነበረው አዋጅ እስከ 100 ሺህ ብር ዓመታዊ ሽያጭ ያለው ደረጃ ሐ ግብር ከፋይ ብሎ ነበር የሚያስቀምጠው፡፡ አሁን ግን እስከ 500 ሺህ ብር ተብሎ ተሻሽሏል፡፡ የበፊቱ አዋጅ የደረጃ ለ ግብር ከፋይ ከ100 ሺህ ብር በላይ ከ500 ሺህ ብር በታች ነበር፡፡ አሁን ግን ከ500 ሺህ ብር በላይ እስከ አንድ ሚሊዮን ብር ሆኗል፡፡ ደረጃ ሀ ከ500 ሺህ ብር በላይ ነበር በአዲሱ አዋጅ ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ ሆኗል፡፡ ስለዚህ ይህንን ታሳቢ ያደረገ የደረጃ ምደባ መደረግ የግድ ብሏል፡፡ ይህ የደረጃ ምደባም በ2003 ዓ.ም በነበረው መረጃ ሳይሆን አሁን በተጨባጭ ባለው መረጃ መሰረት ነው፡፡ ምክንያቱም ቢዝነስ በባህሪ ያድጋል ባለበት ይቆማል ወይም ደግሞ ወደ ኋላ ሊመለስ ስለሚችል እንደ አዲስ ታይቷል፡፡

ሌላው ደግሞ የገንዘብ የመግዛት አቅም ነው፡፡ በ2003 ዓ.ም የነበረው የገንዘብ የመግዛት አቅም አሁን ካለው የተለየ በመሆኑ እንደ አዲስ ስራው ተከናውናል፡፡ ለደረጃ ሐ የተሰበሰበውን መረጃ ወዲያውኑ እንጠቀምበታለን”” ምክንያቱም የቁርጥ ግብር ከፋዮች ናቸው፡፡ የሂሳብ መዝገብ የማቅረብ ግዴታ በህጉም አልተቀመጠም፡፡ አይገደዱም፡፡ የደረጃ ሀ እና የደረጃ ለ ግብር ከፋዮች ግን የሂሳብ መዝገብ የማቅረብ ግዴታ አለባቸው፡፡ ስለዚህ አማካይ የቀን ገቢ ግምት መረጃው ለደረጃ ሀ ና ለ የሂሳብ መዝገብ መረጃ ካላቀረቡ በዚሁ መረጃ የግብር አወሳሰን ስርዓቱ ይከናወናል፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ ያቀረቡት የሂሳብ መዝገብ በባለስልጣኑ በህገ አግባብ ተቀባይነት ከአጣ እና አማካይ የቀን ገቢ ግብር ትመና መረጃ መጠቀም አስፈላጊ ነው ብሎ ተቋሙ ካመነ ይጠቀምበታለ፡፡ ሂደቱ ከዝግጅት ምዕራፍ ጀምሮ ትግበራ ምዕራፍን በዚህ መልኩ ማየት ይቻላል፡፡

ህዳሴ፡- አማካይ የቀን ገቢ ትመናው በየሶስት ዓመቱ መሆን ሲገባው የተራዘመበት ምክንያት ምንድን ነው?
አቶ አትክልት፡- የቀን ገቢ ግብር ትመናው በየሶስት ዓመቱ መሰራት ሲገባው ለ6 ዓመት የተራዘመው የከተማ አስተዳደሩ እና የተለያዩ ኮሚቴዎች በጋራ ተቀናጅተው የሚሰሩት ስራ በመሆኑ የተመቻቸ ጊዜ ስለሚያስፈልግ ነው፡፡ ሌላው ምክንያት ደግሞ አዲሱ የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅም ይጠበቅ ነበር፡፡ እንደሚወጣ ይታወቅ ስለነበረ ማለት ነው፡፡

ህዳሴ፡- እስከ አሁን ሲደረግ ከነበረው የቀን ገቢ ትመና የዘንድሮው በምን መልኩ ይለያል?

አቶ አትክልት፡- ከእስካሁኑ የቀን ገቢ ግብር ግምቶች ለየት የሚያደርገው ከአሰራር አንፃር ስንመለከት እራሱን የቻለ ሊመራ የሚችል መመሪያ አልነበረም፡፡ በ1996 ዓ.ም እና ለ2003 ዓ.ም ባደረግነው፡፡ አሁን ግን ራሱን የቻለ ይህን ሊመራ የሚችል መመሪያ ወጥቶለት ነው የተሰራው፡፡ መመሪያ ቁጥር 123/2009 ዝርዝር ነገሮችን ይዟል”” ሌላው ለየት የሚያደርገው ዘንድሮ የሰጠነው ስልጠና ዘርዘር ያለ ነው”” ሰፋ ያለ ጊዜም የተሰጠው ነው የባለሙያዎች ስልጠና ከኤንስፔክሽን ጋር ተያይዞ ባለፉት ጊዜያት በዚህ ደረጃ አልነበረም፡፡ አሁን ግን እንደየ ወረዳው ተጨባጭ ሁኔታ ስፋትና ጥብበት የኢንስፔክሽን ኮሚቴዎች ተቋቁመው ይህንን ስራ የመደገፍ የመከታተል ሰራ ሲሰሩ ነበር፡፡ ሌላው ደግሞ ከከተማ እስከ ወረዳ የተጠናከረ ቅንጅት ነበር፡፡ አስተዳደሩም እራሱ ገብቶበት በተለየ መልኩ ሲደግፍና ሲከታተል ነበር፡፡ በእነዚህ እና በመሳሰሉት ከባለፈው ለየት ይላል ብሎ መውሰድ ይቻላል፡፡

ህዳሴ፡- በከተማችን ምን ያህል ግብር ከፋይ ነጋዴ ይገኛል? ከፍተኛ፣ መካከለኛና ዝቅተኛ ብለው ቢገልፁልን?
አቶ አትክልት፡- በከተማችን ወደ 331 ሺህ ግብር ከፋዮች አሉ”” ከእነዚህ ውስጥ ግምት የማይገመትላቸ በመረጃ የሚስተናገዱ አሉ፡፡ አማካይ የቀን ገቢ ግምት መወሰድ አለበት ብለን የተንቀሳቀስንባቸው እስከ 200 ሺህ ይደርሳሉ፡፡ ከእነዚህ ውስጥ 68 በመቶው የደረጃ ሐ ግብር ከፋዮች ናቸው፡፡ 21 በመቶው ደግሞ ደረጃ ሀ ሲሆን ሌላው 11 በመቶ የሚሆነው የደረጃ ለ ግብር ከፋይ ነው፡፡ የእስካሁኑ መረጃ የሚያሳየው፡፡ የአሁኑ ግን ገና እየተሰራ ነው፤ ወደፊት እንገልፃለን፡፡

ህዳሴ፡- የቀን ገቢ ግምት የማይሰራላቸው የትኞቹ ዘርፎች ናቸው?

አቶ አትክልት፡- የማይገመትላቸው ግብር ከፋዮች በግልፅ በስልጠና ማንዋላችን ላይም ተቀምጠዋል፡፡ ለምሳሌ መረጃ የሚገኝባቸው አስመጭና ላኪ ከሆኑ አንገምትም፡፡ ምክንያቱም ሲያስመጣና ሲልክ መረጃ እናገኛለን”” ስራ ተቋራጮ ውል አላቸው፣ የኮንስትራክሽን መሳሪያ ኪራይ፣ መኪና ማከራየት፣ አማካሪነት፣ አስጎብኝና የጉዞ ወኪል፣ የውጪ አገር ስራና አሰሪ አገናኞች፣ ትራንስፖርትም የቁርጥ ግብር ከፋይ ነው፡፡ ይህን ያህል መጫን የሚችል መኪና ይህን ያህል ይከፍላል ተብሎ ተለይቷል”” ወፍጮ ቤቶችም ይህን ያህል ቋት ያለው ይህን ያህል ይከፍላል ተብሎ ተቀምጧል፡፡ በመሆኑም አማካይ የቀን ገቢ ግብር ትመና መረጃ መሰብሰብ የሚያስፈልገው ከነዚህ መሰል ዘርፎች ውጪ ለተመሰማሩ ነጋዴዎች ነው፡፡

ህዳሴ፡- በግብር ትመና ስራው ያጋጠሙ ችግሮችስ ምን ምን ናቸው? እንዴትስ ተፈቱ?

አቶ አትክልት፡- በአማካይ የቀን ገቢ ግምት መረጃ አሰባሰብ ያጋጠሙ ችግሮች በራሳችን ላይ በነበሩ ክፍተቶች አንደኛው በቀን በአንድ ቡድን ከ20 እስከ 25 ለሚሆኑት ነጋዴዎች አማካኝ የቀን ገቢ ግምት እንሰራለን ብለን ነበር ነገር ግን ከ7 እስከ 10 ነው አፈፃፀማችን”” በአንድ ወር ውስጥ እናጠናቅቃለን ባልነው መሰረት ለመጓዝ አዳጋች ነበር፡፡ ሁለተኛው ችግር በአማካይ የቀን ገቢ ግምት ሰብሳቢው ቡድን የሚሞሉ ቅፆችን በአግባቡ ያለመሙላት ችግር ይታይ ነበር፡፡ ወደ መረጃ ቋትም በየእለቱ እንዲገባ መመሪያው ያዝዝ ነበር፡፡ ማንጠባጠቦች ነበሩ፡፡ የኢንስፔክሽን ቡድኑ የድጋፍና ክትትል አግባብም በጠንካራ ዲሲፕሊን እንዲመራ ካስቀመጥነው አንፃር የተወሰነ ክፍተት ታይቷል፡፡ ገምግመን የማስተካከያ እርምጃ ወስደናል፡፡ ሌላኛው በግብር ከፋዩ ህብረተሰብ ያጋጠመን ችግር ነው”” ለሽያጭ የተዘጋጁ እቃዎችን መሰወር፣ ሱቆችን ማሳነስ፣ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ትክክለኛ መረጃ እንዳያገኝ የተለያዩ እንቅፋቶችን መፍጠር፣ ህፃናትን ማስቀመጥ፣ ቋንቋውን የማይናገሩ ልጆችን ማስቀመጥ፣ ሱቅ ዘግቶ መጥፋት የመሳሰሉት ተስተውለዋል፡፡

የግብር ከፋዮች አደረጃጀቶችም ስለነበሩ ከነሱ ጋር በመነጋገር ችግሩ ትርጉም ባለው መልኩ እንዲፈታ አድርገናል፡፡ የተወሰኑ ግለሰቦች ግን ተደጋጋሚ ስላስቸገሩ አማካኝ የቀን ገቢ መረጃውን ቀደም ብለንም አይተን ስለነበር በዚያ መሰረት ሰርተናል፡፡ ግብር ከፋዩ ቅሬታ ካለበት በህግና ስርዓቱ መሰረት አቅርበው የማታይ ይሆናል፡፡ አማካይ የቀን ገቢ ግብር መረጃ መሰብሰብ የጀመርነው ሚያዚያ 17 ነው፡፡ ነገር ግን ቡድኖቹ ቀደም ብለው የሚገምቱት ብሎክ ተሰጥቷቸው የአካል ምልከታ ለሁለት ቀን ያህል ስለ አደረጉ ቢዝነሳቸው ምን ይመስላል የሚለውን ቀድመው መረጃ ወስደዋል፡፡ ይህንን መረጃ መሰረት አድርገው ሰርተውታል፡፡
ህዳሴ፡- ግብር በሚተምኑ ባለሙያዎች በኩል የነበረው የኪራይ ሰብሳቢነት አስተሳሰብና ተግባርስ እንዴት ይገለፃል?
አቶ አትክልት፡- እንደዚህ አይነት ችግሮች አጋጥመዋል፤ በተወሰነ መልኩም ቢሆን፡፡ ‘እኔ ነኝ የምገምተው እንደዚህ አዋጡልን’ የሚሉና መሰል ችግሮች ነበሩ፡፡ ግብር ከፋዮች ወዲያውኑ ለባለ ስልጣን መስሪያ ቤቱ ጥቆማ አድርሰዋል፡፡ ችግር እንዳለባቸው የተጠቆሙትን ከቡድኑ እንዲወጡ የማድረግ ስራ ወዲያውኑ ሰርተናል፡፡ ከዚያም በተቋሙ አሰራ ርመሰረት እንዲጠየቁ እየተደረገ ነው፡፡ መረጃው እየተጣራ ማለት ነው”” መመሪያውም በዚህ አግባብ ስላስቀመጠ፡፡

ህዳሴ፡- የኪራይ ሰብሳቢነት አስተሳሰብና ተግባርን ለመከላከል ተቋሙ ምን አይነት አሰራር ዘርግቶ ተንቀሳቅሷል?

አቶ አትክልት፡- አሰራሩ በመመሪያ ቁጥር 123/2009 በግልፅ ተቀምጧል፡፡ ፀብ፣ ዝምድና ካለ ወዲያውኑ አሳውቆ ከኮሚቴው አባልነት የመውጣትና በሌላ አካል እንዲገመት የመጠየቅ መብት ለፈፃሚውም ለግብር ከፋዩም ተመላክቷል፡፡ ግብር ከፋዩም እከሌ ከኔ ጋር ዝምድና አለው ወይም ፀብ አለው ስለዚህ መገመት አይችልም የማለት መብት አለው፡፡
ከዚህ አሰራር ከተላለፈ ደግሞ የሰራተኛ አስተዳደር ህግ አለ፡፡ በዚያ አግባብ የሚጠየቅበት ግልፅ አሰራር ተዘርግቶ ወይይት ተደርጎበት
እናአምኖበት ነው የገባው፡፡ በተግባር ደግሞ ቅድመ እንዳልኩት ኪራይ ለመሰብሰብ ጥረት ያደረጉ አካላት ነበሩ፡፡ ከቡድኑ የማውጣትና በህግ አግባብ ተጠያቂ የማድረግ ስራ እየተከናወነ ነው፡፡ ስለዚህ ለኪራይ ሰብሳቢነት አስተሳሰብና ተግባር ተገቢው እርምጃ ቀደም ብሎ በአሰራር መመሪያው ተገልጿል፡፡ ቅፆችን ግልፅ የማድረግ ስራም ጭምር ተሰርቷል፡፡ ቅፅ 001 የሚባለውን ወዲያውኑ ለግብር ከፋዩ እንዲሰጠው ተደርጓል፡፡

ህዳሴ፡- የቀን ገቢ ግብር ትመናው በተያዘለት የጊዜ ገደብ ተጠናቅቋል ማለት ይቻላል?

አቶ አትክልት፡- ሚያዚያ 17 ነው ስራው የተጀመረው፡፡ በ30 ቀን ውስጥ የመጨረስ እቅድ ነበርን፡፡ ማስተካከያ ስንሰራ የተወሰነ ቀን አቋርጠናል፡፡ በ30 ቀናችን አጠናቅቀናል፡፡ በእቅዳችን መሰረት በተያዘለት የጊዜ ገደብ አጠናቅቀናል፡፡
ህዳሴ፡- የቀን ገቢ ትመናውን ህጋዊና ፍትሀዊ ነው ማለት የሚያስችሉ አሰራሮችን በጥብቅ የመከተሉ ጉዳይ እንዴት ተከናወነ?
አቶ አትክልት፡- የቀን ገቢ ግምት ይህን ያህል ያገኛል ብለን በማየት ብቻ ሳይሆን በተለያዩ አመላካቾች በመታገዝ ነው የሚሰራው፡፡ ለምሳሌ ፀጉር ቤት ስንት ወንበር አለው የሚለው ለገቢው አመላካች ነው፡፡ ሌሎች የጥፍር ቀለምና መሰል ቁሳቁሶችን ጎን ለጎን የሚሸጥ ከሆነም ሌላው አመላካች ነው፡፡ ግምት ስለሆነ በተወሰነ መልኩ ችግር አይኖርም ብሎ መውሰድ ባይቻልም እንዳይጎሉ ግን በጥንቃቄ ተንቀሳቅሰናል፡፡ የግል ማስታወሻ በማየት፣ የሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያ በማየት፣ የአካባቢውን ገበያ (መጀመሪያ መንገድ፣ ሁለተኛ መንገድ፣ መጋቢ መንገድ፣ ሶስተኛ መንገድ) በተመሳሳይ አመላካቾች ናቸው፡፡ በመሆኑም በተቻለ መጠን ፍትሃዊ እንዲሆን ተንቀሳቅሰናል፡፡

ህዳሴ፡- አጎራባች ቀጠናዎች በተቀናጀ መልኩ ትመናውን እንዲያስኬዱ ማድረጉስ ምን ይመስላል?
አቶ አትክልት፡- በመመሪያችንም በግልፅ ተቀምጧል፡፡ በተለይ አዋሳኞች አሉ ክፍለ ከተማ ከክፍለ ከተማ ወረዳ ከወረዳ አንዱ መንገድ ከአንዱ መንገድ የሚዋሰኑ አሉ፡፡ ይሄ ጉራማይሌ እንዳይሆን ኮሚቴዎቹ እየተነጋገሩ በጋራ እንዲሰሩ ነው የተደረገው፡፡ ለምሳሌ ቦሌንና የካን የሚሰሩ በአዋሳኝ ቦታዎች ላይ ኮሚቴዎቹ ተናብበው እንዲሰሩ ተደርጓል”” ሌላው ከከተማ እስከ ወረዳ በየጊዜው መረጃው እየተገመገመ በቅንጅት ነው የተሰራው፡፡

ህዳሴ፡- ከዚህ በኋላ የተቋሙ የቀጣይ አቅጣጫ ምንድን ነው?

አቶ አትክልት፡- አማካኝ የቀን ገቢ ግምቱ ለግብር ከፋዩ በደብዳቤ እንዲደርሰው ይደረጋል፡፡ ቅሬታም ካለ ቅሬታውን ያቀርባል፡፡ ይህንን የሚቀበል በየወረዳው የቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ ተደራጅቷል፡፡ በየክፍለ ከተማውም በተመሳሳይ ተዋቅሯል፡፡
ከዚህ በኋላ ወደ ግብር እና ታክስ ወደ መክፈል ይገባል፡፡ ከሀምሌ አንድ ጀምሮ እስከ ጥቅምት 30 የግብርና የታክስ መክፈያ ወቅት ነው፡፡ ከሀምሌ 1 እስከ 30 ደረጃ ሐ ግብርና ታክስ ይከፍላል፡፡ ደረጃ ለ ከሀምሌ 1 እስከ ጳጉሜ መጨረሻ ገብርና ታክሰ ይከፍላል፡፡ ደረጃ ሀ ደግሞ ከሀምሌ 1 እስከ ጥቅምት 30 ግብር እና ታክሱን ይከፍላል፡፡

ህዳሴ፡- በመጨረሻም ለግብር ከፋዩ ህብረተሰብ የሚያስተላልፉት መልዕክት ካለ?

አቶ አትክልት፡- አማካኝ የቀን ገቢ ግብር ግምት መረጃ ሲሰበሰብ በርካታ ግብር ከፋዮቻችን ስራው የተቃና እንዲሆን ከኮሚቴውና ከባለስልጣኑ ጎን ሆነው ላበረከቱት አስተዋጽኦ ምስጋና እናቀርባለን፡፡ መረጃ በመሰወር እና ስራው እንዲደናቀፍ ሲንቀሳቀሱ የነበሩት ደግሞ ግብርን የመክፈልን ሀገራዊ ዓላማ ተረድተው ግዴታቸውን ወደፊትም በአግባቡ እንዲወጡ መልዕክት አስተላልፋለሁ፡፡ ግብር ከፋዮቻችን በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ ግብርና ታክሳቸውን እንዲከፍሉ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ፡፡

ህዳሴ፡- ስለነበረን ቆይታ እናመሰግናለን፡፡
አቶ አትክልት፡- እኔም አመሰግናለሁ፡፡

Tuesday, 27 June 2017

የኦሮሚያ ክልል በአዲስ አበባ ከተማ ላይ ያለውን ህገ-መንግሥታዊ ልዩ ጥቅም አስመልክቶ የቀረበ መግለጫ

 

የኢትዮጵያ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ሰፊ ውይይት ካካሄዱበት በኋላ በተወካዮቻቸው አማካይነት ያፀደቁት ህገ-መንግሥት የሁሉንም ሕዝቦች መብቶችና ጥቅምች የሚያስጠብቅ ነው፡፡

ህገ-መንግሥቱም የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የቃል-ኪዳን ሰነድ ሲሆን ዓላማውም በሕዝቦች መፈቃቀድና ፍላጎት እንዲሁም ዴሞክራሲያዊ አንድነት ለማጎልበት እንዲቻል በጋራ ያፈሯቸው እሴቶችና ሃብቶች እንዲሁም ትስስሮች እንዳሏቸው በማመን- በታሪካቸው ሂደት ውስጥ ያጎለበቷቸውን የጋራ ጉዳዮች ይበልጥ ለማበልፀግና የተዛቡ ግንኙነቶችንም በማረም አንድ ጠንካራ የጋራ ኢኮኖሚያዊ ማህበረሰብ እና የጋራ ፖለቲካዊ ማህበረሰብ ለመገንባትና ለማጠናከር የታለመ ነው፡፡

Tuesday, 13 June 2017

በሳዑዲ በኢትዮጵያውያኑ ላይ የትናንቱ እንዳይደገም



 

 

በአረብ ሀገራት ኢትዮጵያውያን በብዛት ከሚኖሩባቸው ሀገራት አንዷ ሳዑዲ አረቢያ ናት።

 በሀገሪቱ በየአመቱ የሚካሄዱ ሃይማኖታዊ ስነስርአቶችን ጨምሮ በልዩ ልዩ መንገዶች ወደ ሀገሪቱ የሚገቡ ዜጎች በህጋዊም ሆነ የሀገሪቱን ህግ ተላልፈው ለአመታት ሲኖሩባት የቆችው ይህቺ ሀገር፥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በውጭ ሀገራት ዜጎች ዙሪያ ጠንካራ ህጎችን በማውጣት እርምጃ እየወሰደች የምትገኝ ሀገር ሆናለች። እንደ ሌሎች ሀገራት የውጭ ዜጎች በልዩ ልዩ የስደት ሰበቦች በሀገሪቱ ለመኖር ቢፈልጉ ይህንን የሚያስተናግድ ህግ የላትም። በአብዛኛው ከተለያዩ ሀገራት ወደ ሀገሪቱ የገቡ የውጭ ዜጎች ይኖሩባታል።

ኢኮኖሚዋ ከነዳጅ በሚገኝ ገቢ ላይ የተመሰረተው ይህች አገር የምርቱ በዓለም ገበያ ላይ ዋጋው እየወረደ መምጣት ፈተና ሆኖባታል። ይህንን ተፅእኖ ለመቋቋም የመንግስት የወጪ ቅነሳን የሚያበረታቱ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን አዘጋጅታ በመተግበር ላይ የምትገኝ ሲሆን፥ ስራ አጥ ለሆኑ የአገሬው ሰዎች የስራ እድልን ያመጣሉ ያለቻቸውን እርምጃዎችንም ስትወስድ ቆይታለች። ከእነዚህ እርምጃዎች መካከል በተለይም በአገልግሎት ዘርፎች ላይ የሚገኙ ስራዎች ያለ አግባብ በውጭ አገራት ዜጎች ተይዘዋልና እነዚህን የስራ እድሎች ለሳዑዲ ዜጎች ክፍት ሊደረጉ ይገባል ይላሉ ፖለቲከኞቿ። ይህ እንዲሆን ህጋዊ ሰነድ የሌላቸውን የተለያዩ አገራት ዜጎች ከግዛቷ ማስወጣትን እንደ አንድ አማራጭ በመያዝ በተለያዩ ጊዜ በዘመቻ ስታስወጣ ቆይታለች።

Wednesday, 24 May 2017

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ሕገ-መንግስት መሰረታዊ ዓላማዎች

የኢ... ሕገ-መንግስት የኢትዮጵያ ህዝቦች በሃገራቸው መፃኢ ዕድል ላይ ብሩህ ተስፋ ሰንቀው እንደ አንድ ማህበረሰብ እንዲነሳሱ የሚያደርጋቸውን ዓላማ ያስቀመጠ ነው፡፡ ዓላማዎቹ በህገ-መንግስቱ መግቢያ ላይ የሰፈሩ ናቸው፡ ይህም አጠር ባለ መንገድ ሲገለፅ ያለፈውን የተዛባ ግንኙነት በማስተካከል እና ባለፈው ያፈሩትን የጋራ ሃብት፣ ትስስርና እሴት ስላላቸው በፍላጎታቸውና በራሳቸው ፈቃድ ዘላቂ ሰላም፣ ዋስትና ያለው ዴሞክራሲ እንዲሰፍን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እድገታቸው እንዲፋጠን የሚያስችል የጋራ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ማህበረሰብ ለመገንባት ቃል የገቡ መሆናቸውን፣ ይህን ለማሳካት የግለሰብም ሆነ የብሄሮች ብሄረሰቦች ህዝቦች መብቶችና የፆታ እኩልነት ማረጋገጥ፣ ባህሎችና ሃይማኖቶች ያለ አድሎና ልዩነት እንዲራመዱ ማድረግ ፅኑ እምነታቸው እንደሆነ መወሰናቸውን …. የሚል ነው፡፡ የሕገ-መንግስታችን መግቢያ ዘላቂ ሰላም፣ ዋስትና ያለው ዴሞክራሲ፣ ፈጣን ኢኮኖሚያዊ ልማት፣ አንድ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ግንባታ የሚሉ ዓላማዎችና ራዕዮች በግልፅ አስቀምጧል፡፡ እነዚህ የህገ-መንግስታችን ዓላማዎች የማይነጣጠሉና እርስ በርሳቸው የተሳሰሩ ናቸው፡፡

Tuesday, 1 November 2016

‹‹ እየታደስን እንሰራለን እየሰራን እንታደሳለን›› ነው





1.ግሮቻችንን ያለምህረት እንገምግም፣ ከችግሮቻችን እንቆራረጥ

2009 በድርጅታችን ኢህአዴግ ሰፊ ዳግም በጥልቀት መታደስ ንቅናቄ የሚካሄድበት መሆኑ ይታወቃል፡፡ በጥልቀት መታደስ ለምን አስፈለጊ ሆኖ እንደተገኘም በቂ የህዝብ ግንኙነት ስራ ተሰርቷል ማለት ይቻላል፡፡ መዋቅራችን ብቻ ሳይሆን በጥልቀት መታደስ ለምን አስፈለገ በሚለው ዙሪያ በህዝብ ኮንፈረንስም መግባበት ለመፍጠር ጥረት ተደርጓል፡፡ አሁን በምንገኝበት ድርጅታዊና ሃገራዊ ሁኔታ ጉዟችንን ሊቀለብሱ የሚችሉ ፖለቲካዊ ብልሽቶች አጋጥመውናል፡፡ ይህንን ሲባል ግን ግምገማው እስካሁን ለመጣነው ጉዞና ለተገኙ ድሎች በዜሮ የሚያጣፋ መሆን የለበትም፡፡
ነባራዊ ሁኔታው ስንገመግም መነሻችን እና አተያየታችን የተዛባ መሆን የለበትም፡፡ ያጋጠሙን የውስጥ ድርጅትና ሀገራዊ ተግዳሮቶችና እንቅፋቶች በስኬቶች ላይ ሆነን ያጋጠሙን ናቸው የሚለውን የድርጅታችን ግምገማ በጥብቅ መጨበጥ ይገባል፡፡ በመሆኑም በጥልቀት መታደስ አለብን ሲባል ከችግሮቻችን መቆራረጥ አለብን ማለት እንጂ እስካሁን ያሳካናቸው ስራዎቻችንን የሚደፈጥጥና የሚክድ መሆን አለበት ማለት አይደለም፡፡ በጥልቀት መታደስ አስፈላጊ የሆነው እሰካሁን የረባ ስራ ስላልሰራን ይህንን ሀጥያት ለመናዘዝ ሳይሆን በስኬት ላይ ሆነን ያጋጠሙን ችግሮች ግን አቃልሎ መታየት የሌለባቸው ብቻ ሳይሆኑ በተለየ የተሃድሶ ንቅናቄ መልክ በፍጥነት ካልቀለበስናቸው አጠቃላይ ድሎቻችንም የሚበሉ የህዳሴ ጉዟችንም የሚያደናቅፉ ከባድ ችግሮች  ናቸው፡፡ የመጀመሪያው ሊሰመርበት የሚገባና መግባበት ሊደረስበት የሚገባ ነጥብ ይህ ነው፡፡

Wednesday, 24 August 2016

ከቀለም አብዮት በስተጀርባ (behind the color revolution) የተደበቁ ቁማርተኞች





I. የቀለም አብዮት (color revolution) መነሻ ምክንያቶች

እንደ አውሮፓ አቆጣጠር በ1991 ዓ ም የተባበሩት የራሽያ ሶሺያሊስት ሪፓብሊክ ሀገራት ሲበታተኑ ከከረረ የአይዲዮሎጂ ልዩነት ጋር በዓለም ሁለት ኃያላን ሀገራት ተፈጠሩ። እነዚህ ኃያላን የሩሲያ የልማታዊ መንግሥት አስተሳሰብ ጎራና የአሜሪካ የገብያ አክራሪ አራማጅ ኃያላን ጎራዎች ናቸው። ሁለቱ ጎራዎች ሌሎች ሀገራትን በተጽዕኗቸው ሥር ለማስገባት የሚያደርጉት ጥረትና ድካም እንደ ተጠበቀ ሆኖ የአሜሪካና የምዕራብ አውሮፓ ኃያላን ዓለምን በሙሉ በአንድ የገብያ አክራሪነት ካምፕ ውስጥ ለማስገባት በተለያዩ ዘዴዎች አንዱን ከሌላው እያጋጩ በማተራመስ ዘዴ ሠርገው ለመግባትና የኃሳብ የበላይነታቸውን ለመጫን ብዙ ሞክረዋል፣ እስከ ዛሬም ቀጥለዋል።
በሌላ በኩል የመንግሥታዊ ካፒታሊዝም ባህሪን ይዞ የቀጠለውና በኋላም በዲንግ ምፒንግ ጠንካራ አመራር እየዳበረ የመጣው የቻይና ልዩ ፖለቲካል ኢኮኖሚ የገብያ አክራሪ አስተሳሰብን እንደ ወረደ ሳይቀበል በራሱ ተጨባጭና ነባራዊ ሁኔታ አስተካክሎ በመቀጠሉ ተአምራዊ በሆነ ፍጥነት እያንሠራራ ቀጠለ። በሩሲያም በኩል በተለይ በብላድሚር ፑቲን አመራር የራሱን ተጨባጭ አቅም መሠረት ያደረገ ልማታዊ ባህሪን አጠናክሮ በመቀጠሉ አሁንም ዓለም በአንድ የፖለቲካል ኢኮኖሚ ዋልታ ልትመራ እንደማትችል የሚያሳይ ክስተት እያቆጠቆጠ መጣ። ያልተጠበቁ እና የተለያዩ ባህርያት ያሏቸው የኢኮኖሚ ዋልታዎች የመሥፋፋት ክስተት በሌሎችም የምሥራቅ እስያ ሀገራት እያንሠራራ መምጣቱን ተከትሎ ሌሎች ሀገራት ወደእነዚህ አዳዲስ ዋልታዎች ጎራ እንዳይቀላቀሉ የቀለም አብዮት አጀንዳን መጋበዝ ጀመሩ።

Tuesday, 19 July 2016

ታዳጊ ዴሞክራሲያችን የሚጐለብተው መቻቻልን በሚቀበል ህብረተሰብ ነው ክፍል 2 (በሓጎስ ገ/ክርስቶስ )

. ዴሞክራሲያዊ የአስተሳሰብ ትግል በማጎልበት ጠባብነትና ትምክህተኝነትን እንመክት

ታዳጊ ዴሞክራሲያችን የሚጐለብተው መቻቻልን በሚቀበል ህብረተሰብ ነው

በመጀመርያ ክፍል ፅሑፌ ጠባብነትና ትምክህተኝነትን የምንዋጋው በዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብ መሆኑ፣ የዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብ እሴት ከሆኑት መካከል ደግሞ አንዱ ምክንያታውነትን የመቀበል፣ በህግጋተ ምክንያታውነት መመራት እንደሆነ ለመግለፅ ተመኩራል፡፡ በፅሑፉ ዙርያ የተሰጡ አስተያየቶች ገምቢ ሐሳብን በገንቢነቱ፣ አፍራሽ ሐሳብ ደግሞ በአፍራሽነቱ ለመረዳት፣ ከገንቢ አስተያየቶችን ሁሌም እንደማደረገው ትምህርት ለመውሰድ ችያለሁኝ፡፡
የሐሳብ ነፃነት ለዜጐች የተሠጠ መብት መሆኑን በመረዳት፣ ሐሳብ የመግለፅ መብትም እንደገበያ የሚመስል፣ በገበያ የሚጠቅምህንና የሚያስፈልግን በገበያ ህግጋተ የመግዛት፣ የማያስፈልግህንና የማይጠቅምህን ደግሞ በገበያ ህግጋት እንደመተው አድርጌ ለማዛመድ ጥረት በማድረጌ በዚህ አጋጣሚ የሽንፈትና የፀረ-ዴሞክራሲ ምልክቶችና የአሮጌ አስተሳሰብ አራማጅ የሆኑትን አስተያየቶችን አይቼ አላየኋቸውም፣ ሰምቼም አልሰማኋቸውም፡፡ ከተሳዳቢዎች ጋር መሳደብ ማርን በኮሶ እንደመብላት ተደርጐ የሚወሰድና ከአንድ በ21ኛው ክፍለ ዘመን የተፈጠረ የህዳሴው ትውልድን የማይጠበቅ በመሆኑ በግሌ አያሳክከኝም፡፡ ስድብ የዴሞክራሲ የመጨረሻ የዘቀጠ አተላ በመሆኑንም ዛሬም ነገም አተላ የመጨለጥ ባህሪ አይኖርብኝም፡፡ እናም የክፍል ሁለት ዋናው ጭብጥ ከመግባቴ በፊት የ21ኛው ክፍለ ዘመን ትውልድ ነኝ የሚል ሰው ሐሳብን በሐሳብ የመመጐት ባህል ማዳበር ይኖርበታል በሚል ጥቆማየን አቀርባለሁ፡፡
ዴሞክራሲ ስር ሊሰድ የሚችለውንና ተኮትክቶ ሊያድግ የሚችለው በምክንያታዊነት ከሚያምን ህብረተሰብ ባሻገር መቻቻልን ቅቡል ያደረገ ህብረተሰብ ጭምር ሲፈጠር እንደሆነ እሙን ነው፡፡ መቻቻልና የመቻቻል እሴቶችን መተግበር በማይቻልበት ሁኔታ አስተማማኝ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ማስፈን አይቻልም፡፡ መቻቻል በሌለበት ዴሞክራሲ ያድጋል ብሎ ማሰብ ውሃን በድንጋይ እንደማፍሰስ ነው፡፡ መቻቻል ባልተፈጠረበት ሁኔታ ዴሞክራሲ በአስተማማኝ ደረጃ ይገነባል ብሎ ማሰብ በምድረባ ስንዴ እንደማብቀል ነው፡፡ እንደኛ በመሰሉ በዕድገት ላይ የሚገኙ ሃገራትና በርካታ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ባለበት ሁኔታ ደግሞ የመቻቻል ትርጉም የላቀ ነው፡፡ የተለያየ ሃይማኖትና እምነት ተከታይ የሆነ ህዝብ ባለበት ሃገር የሃይማኖት ነፃነትን፣ የሃይማኖት እኩልነትን እንዲሁም የመንግስትና ሃይማኖት መለያየትን መቀበል መሰረታዊ ነው፡፡ የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች እናት በሆነች ሃገር በተለያዩ ብሄር በሄረሰቦችና ህዝቦች የሚነገሩ ቋንቋዎች ማክበርና ማስከበር መሠረታዊ ነው፡፡ የብሄር ብሄረሰብና ህዝቦች ባህል፣ እሴቶችን እንዲሁም ማንነትን ቅቡል አድርጐ ተቻችሎ የመኖር ጉዳይ ለሃገራችን ህልውና መሰረታዊ ነው፡፡
የመቻቻል ጉዳይ የባህል፣ የሃይማኖት፣ የቋንቋ፣ የትውፊት ልዩነትን የመቀበል መሆኑን፣ መቻቻል ሲባል የሐሰብ ልዩነትን በዴሞክራሲያዊ መንገድ የማስተናገድ፣ የሐሳብ ክርክርን በሰለጠነ መንገድ የማስተናገድ ጉዳይ ነው፡፡ መቻቻል ሲባል ምንም ዓይነት የሐሳብ ትግል የሌለበት ማለት ሳይሆን በተለያዩ ግለ-ሰዎችም፣ ድርጅቶችም የሚነሱ ሐሳቦችን ለማዳመጥ ዝግጁ የመሆን፣ እኔ ከያዝኩት ውጪ በሚል ፈሊጥ በስነ-ልቦናና በተግባር ለመቀበል ዝግጁና ፍቃደኛ አለመሆን ደግሞ ለፀረ-መቻቻልን መቆምን ማለት ነው፡፡ እኔ ያልኩትን ሁሌም ትክክለኛ ነው፤ በእኔ ከሚራመደውን አቋም በተለየ መንገድ የማራመድ ጉዳይ በእኔ መቃብር ነው የሚል ፈሊጥ የዴሞክራሲያዊ እሴት የሆነውን መቻቻል ከመግደል ውጪ የሚፈይደው ነገር የለውም፡፡ ሊኖርውም አይችልም፡፡
ሲጠቃለል ዴሞክራሲያዊና ገምቢ መቻቻል በውስጠ ድርጅት፣ መቻቻል በስራ ቦታ፣ መቻቻል በምንኖርበት አከባቢ፣ መቻቻል በምንማርበት ትምህርት ቤት ከዴሞክራሲ አንፃር ፋይዳው የጐላ ነው፡፡ መቻቻል በህዝብ ታሪክ ዙርያ ትልቅ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ነው፡፡ ከዚህ አኳያ አንድን ብሄር በኢትዮጵያ የተለየ ታሪክ ሰሪ፣ የኢትዮጵያ አንድነት ጠበቃ፣ የስልጣኔ ባለቤት፣ ሌላኛው ደግሞ ለኢትዮጵያ ፀረ-አንድነት የቆመ፣ ታሪክ የሌለው ወይም ከሌሎች ኢትዮጵያውያን በተለየ መንገድ ተጠርጣሪ አድርጎ የማየት አዝማምያ በህዝቦች ታሪክ ላይ ያለው የተዛባ የታሪክ አለመቻቻል ተደርጐ የሚወሰድ ነው፡፡ መቻቻል የሐሳብ ልዩነትን መቀበልና ማክበር ነው፡፡ መቻቻል የባህል ልዩነትን መቀበልና ማክበር ነው፡፡ መቻቻል የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦችን ቋንቋ፣ ባህል፣ ሃይማኖት፣ እሴቶች፣ ታሪክ፣ ልዩነትን መቀበልና ማክበር ነው፡፡
በአንፃሩ በቀደምት ስርዓቶች ተመኩሮ ሃገራችን ለብተና ዳርጓት የነበረውን የአንድ ባንዴራ፣ አንድ ሃይማኖትና አንድ ቋንቋ የጥቂት ትምክህተኞች ቀረርቶና የመቻቻልን እሴት የሚያጠፋ ነው፡፡ ባለፉት ሁለት 10 ዓመታት እየተገነባ ያለውን የዴሞክራሲያዊ ብሄርተኝነትን አስተሳሰብ ቅቡል አድርጐ አለመውሰድ፣ የብሄር ብሄረሰቦችንና ህዝቦችን ባህል፣ ቋንቋ፣ ትውፊቶች ለመጨፍለቅ (Assimilate) ለማድረግ የሚደረግ በመሆኑ ፀረ-መቻቻልና በባህሪው ፀረ-ዴሞክራሲ ነው፡፡ የህገ-መንግስቱ ትርፋት፣ የሰላማችን ምንጭ የሆነውን የዴሞክራሲያዊ ብሄርተኝነት አስተሳሰብን የሚቀበል ሃይል በፀረ-ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብና ብብዕር ቢጤ ለማሸማቀቅና ለማጥቃት መሞከርም ከጠባብና የትምክህት ሃይሎች የሚጠበቅ ቢሆንም ፀረ-የሐሳብ መቻቻልና ፀረ-ዴሞክራሲያዊ ነው፡፡በድምሩ ጠባብነት ብሎ መቻቻል አይታሰብም፣ ጠባብነት ጅብ ለጅቡ እንኳን የሃገሬ ጅብ ይብላኝ የሚል፣ በጅቦች መካከል የጐጡን ጅብ የሚመርጥ እስከሆነ ድረስ በሰኒ አስተሳሰቡ ተወስኖ የሚኖር እና በሰኒ ውስጥ የሚዋኝ እንጂ መቻቻልን የሚጠብቅ እንዲሁም የመቻቻልን እሴት የሚቀበል አይደለም፡፡
በተመሳሳይ ትምክህት ብሎ ስለ መቻቻል ማሰብ በምንም ተአምር አይታሰብም፡፡ የዴሞክራሲያዊ ብሄርተኝነትን አስተሳሰብ ፈፅሞ ለመቀበል ባልተቻለበት፣ የማንኛውም ብሄር በሄረሰብና ህዝቦች የቋንቋ፣ የባህልና የትውፊት ልዩነት መቀበል “አንድነት ወይም ሞት” በሚል ፈሊጥ የትምክህት ሊቀ-ሊቃውትነት ለመሆን ሽርጉድ በሚባልበት፣ ኢትዮጵያ ሁሉም ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ተቻችለው ሊኖሩባት የምትገባ የብዙሃነት ሃገር ናት በሚባልበት “ጃ” በሚዘመርበት ሁኔታ መቻቻል አይታሰብም፡፡ “ጃ” ና “ጥቁር ሰው” ብሎ መቻቻል የለም፡፡ “ጃና ጥቁር ሰው” ብሎ አንድ ላይ ጨፍልቆ መግዛት (Assimilation policy) ነው ያለው፡፡ በ “ጃ”ም “ጥቁር ሰውም” ውስጥ አሁን ያለውን የዴሞክራሲያዊ እሴት ተደርጐ የሚወሰደውን መቻቻል ብሎ አይታሰብም ፡፡ በመሆኑም ጠባብነትና ትምክህተኝነት አመለካከት ነው፡፡ የተዛባ አመለካከት ደግሞ የሚስተካከለው በመጥረብያ ሳይሆን በዴሞክራሲያዊ የሐሰብ ትግል ነው፡፡ መጥረብያ በመጠቀም የጠባብነትና ትምክህት አመለካከት ችግር እንቅረፍ ብንል በንድፈ ሃሳብም በተግባርም አይቻልም፡፡ ከዴሞክራያዊ ባህርያችን አንፃርም ፈፅሞ ተቀባይነት የለውም፡፡
በተመሳሳይ ጠባብነትና ትምክህት እንደ ፀረ-ኩፍኝ በሽታ በክትባት የምንከላከላቸው አይደሉም፡፡ ዋናው የመከላከያ መድሃኒቱ ዴሞክራሲያዊ የአስተሳሰብ ትግል መሆኑን፣ መልሶ መላልሶ ማስተማር መሆኑን፣ የመቻቻል እሴትን ሊቀበል የሚችል ህ/ሰብ የመፍጠር ጉዳይ መሆኑን፣ ይህ ለማድረግም የስነ-ዜጋና ስነ-ምግባር ትምህርት ወሳኝ መሆኑን፣ ዴሞክራሲያዊ የሆነ ሚድያም ከዚሁ አንፃር የላቀ ሚና ያለው መሆኑን መረዳት ተገቢ ነው፡፡
ጠባብነትና ትምክህት አመለካከት ነው፣ ጠባብነትና ትምክህት ተከትሎ የሚወረወረው ድንጋይ ይሁን ጥይት አመለካከቱ የወለደው ነው፡፡ ድርጊቱ ፍፁም ፀረ-ዴሞክራሲ ነው፡፡ መድሃኒቱም የዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብ ትግል ነው፡፡ የተሻለ መድሃኒቱም የዴሞክራሲያችን እሴት የሆነውን መቻቻል ማጐልበት ነው፡፡ በእኛ ተጨባጭ ሁኔታ መቻቻል ማለት የዴሞክራሲያዊ ብሄርተኝነት አስተሳሰብ እንዲጐለብት መጣርና መረባረብ ማለት ነው፡፡ ይህ የሚገኘውም በእልህ ሳይሆን የዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብ ስበእናና ትጥቅ በመያዝ ነው፡፡ የዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብ እሴት የሆነውን መቻቻልን በማጠናከር ነው፡፡
ክፍል 3 ይቀጥላል

Saturday, 16 July 2016

ዴሞክራሲያዊ የአስተሳሰብ ትግል በማጎልበት ጠባብነትና ትምክህተኝነትን እንመክት (በሓጎስ ገ/ክርስቶስ ክፍል 1)



ዴሞክራሲያዊ የአስተሳሰብ ትግል በማጎልበት ጠባብነትና ትምክህተኝነትን እንመክት
1.1.ታዳጊ ዴሞክራሲያችን የሚጎለብተው በምክንያታዊነት የሚያምን ሕብረተሰብ በመፍጠር ነው
በሓጎስ /ክርስቶስ
ክፍል 1
የኢትዮጵያ ህዝቦች አሁን የተገኘውን የፖለቲካ ስልጣን ባለቤት ለመሆን ያካሄዱት መራራ ተጋድሎና የከፈሉት መስዋእትነት እጅግ ውድ መሆኑን ግልጽ ነው ፡፡ የዜጎችና የቡድን መብቶች እንዲከበሩ ፣ዘላቂና አስተማማኝ ዋስትና ያለው ሰላም እንዲሰፍን መራራ ተጋድሎ አካሂደዋል ፡፡ ክቡር ህይወታቸውና አካላቸውም ገብረዋል ፡፡ በዚህም ሰው በላ የደርግ ስርዓት ግብአተ-መሬት እንዲገባ በማድረግ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች የስልጣን ባለቤት የሆኑበት ዴሞክራሲያዊ ህገ-መንግስታዊ ስርዓት ተገንብቷል ፡በቀጣይነት እተገነባም ይገኛል ፡፡
እየተገነባ ያለው ስርዓት ሁሉም ብሄር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ተጠቃሚ ያደረገ ስርዓት ነው ፡፡ እየተገነባ ያለ ስርዓት በብሄሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች መልካም ፈቃድ የተመሰረተ የቀደምት ስርዓቶች ኋላ ቀርና አድሃሪ አመለካከትን በመሰረታዊ መልኩ አሽቀንጥሮ የጣለ ስርዓት ነው ፡፡ የተጀመረው ዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ በኢትዮጵያውያን ላይ ተበይኖ ነበረውን ፀረ-ዴሞክራሲያዊ ልጓም የፈታ ፣ኢትዮጵያ የጥቂቶች ሳትሆን የሁሉም ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች አገር ያደረገ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ነው ፡፡ አሁን እየተገነባ የሚገኘው ታዳጊ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት የቀድሞ ስርዓት እንደ ሃጥያት ሲመለከቱት የነበረውን የብሄር ብሄረሰቦችንና ህዝቦች ፣የሃይማኖት እኩልነት እና ነጻነትን ያረጋገጠ ስርዓት ነው ፡፡
እየተገነባ ያለው ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት የግዛት አንድነት አስተሳሰብን በመናድ በምትኩ በመፈቃቀድ ላይ የተመሰረተችውን የህዝቦች አንድነት የተቀበለና እየተገበረ ያለ ስርዓት ነው ፡፡ ለብተና ለመዳረግ አፋፍ ላይ የነበረችውን ሃገራችን ከብተና እና እልቂት ያተረፈ ስርዓት ነው ፡፡ የህዝቦችና የዜጎች ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እስርቤቶችን በማፈራረስ የሁሉም ኢትዮጵያውያን ሆነች ሃገር የገነባና በመገንባት ላይ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ነው ፡፡ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ራሳቸውን በራሳቸው እንዲያስተዳድሩ ፣በቋንቋቸው እንዲማሩ እና እንዲዳኙ ፣በባህላቸውና ማንነታቸውን እንደኮሩና እንዲያሳድጉ በጋራ ጉዳያቸው ደግሞ ህገ-መንግስቱ በሚፈቅደው በሚዛናዊ ውክልና በጋራ እንዲወስኑ ያስቻለ ስርዓት ነው ፡፡
ሲጠቃለል ዴሞክራሲያዊና ፌዴራላዊ ስርዓታችን ባለፉት 25 ዓመታት በፖለቲካ፣በማህበራዊና በኢኮኖሚ መስኮች ሃገራችን ከነበረችበት የቁልቁለት ዕድገት አውጥቶ ሽቅብ እንድትወጣ ያደረገ ስርዓት ነው ፡፡ የድህነት ተምሳሌት በመሆን በድህነትና ኋላ ቀርነት ማዕበል ስትናወጥ የነበረችውን ሃገራችን አረጌውን ታሪክ በመቀየር በፈጣን የዕድገት ባቡር እንድትጓዝ ያስቻለ ስርዓት ነው ፡፡ የድህነት ውቅያኖስን በዴሞክራሲያዊና ልማታዊ መስመር እየቀዘፈ በዕድገት ገናና ሃገር ለመፍጠር እየተንቀሳቀሰ ያለ ስርዓት ነው ፡፡ በሃገራችን እየታየ ያለ ስኬትም ትክክለኛ የሆነ መስመር ፣ህገ መንግስትና ህገ መንግስታዊ ስርዓት ስለ ተረጋገጠና የህዝቦች ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ስለተረጋገጠ ነው፡፡
ይሁን እንጂ ምክንያታዊ ካለመሆን የተነሳ በሃገሪቱ ያለውን ተጨባጭ እውነታ የማጣጣል የመጡ ለውጦችን እና ፈተናዎችን ሚዛናዊ ሆኖ በምክንያታዊነት ያለመረዳት ፣ለመረዳት ያለመፈለግ ጨለምተኛ አስተሳሰብ የመያዝ እንዲሁም ለውጡን የመካድ አዝማምያ ይታያል ፡፡ እዛም እዚህም የሚታዩ አለመግባባቶችን ከስርዓቱ የመነጩ ናቸው የሚል የተሳሳተ አመለካከት የመያዝ የዴሞክራሲያዊ ስርዓቱ ትሩፋቶችን የማንኳሰስ አባዜ ይታያል ፡፡ በየአካባቢው የሚፈጠሩ ችግሮች በውስጣችንና በውጪ ባሉ ጥገኛ ሃይሎች መፈጠራቸው ባይካድም ረጋ ብሎ ሁኔታዎችን መተንተን ትርፉና ኪሳራውን በብቃት ያለማስላት ወገንና ጠላትን በበስለት ያለመለየት ፣የጥገኞች ጉዳይ የህዝብ ጉዳይ እንዳልሆነ ፣ጥገኞች በየትኛው አካባቢ በብሄር ስም ለመነገድ ከሚያደርጉት እንቅስቃሴ ውጪ ከያዙት አለማ አንጻር የሚወክሉት ብሄርም ህዝብም እንደሌለ አንድ ምክንያታዊ ሆነ ዜጋ ማሰብ ይኖርበታል ፡፡ ይገባልም ፡፡
እናም በአንድ አካባቢ ችግር ሲከሰት ከችግሩ በስተጀርባ ያለው ማነው ? ለምንድነው እንደዚህ አይነት ፍላጎትና አድራጎት ሊኖረውና ሊፈጽም የቻለው ? በሚል መንፈስ መድረኩ በሚጠይቀው የዴሞክራሲያዊ የትግል አስተሳሰብ በመጠቀም እንዴት መመከት ይቻላል ብሎ ማሰብ ፣መተንተን ፣ጠላትን ከወዳጅ ህዝብና ጥገኞች ፣ድርጅትና በውስጡ የሚገኙ ጥቂት ኪራይ ሰብሳቢዎችን በህግጋተ-ምክንያታዊነት መለየት ፣መታገል እና የዴሞክራሲያዊ ብሄርተኝነት አስተሳሰብ ማጎልበት ይኖርበታል ፡፡ በተለይ የህዳሴው ወጣት በእንዲዚህ አይነት ሁኔታና አጋጣሚ ንፋስ ሽው ወዳለበት በአንድ ሴኮንድ ሽው ሳይል እውነተኛውና የጥፋት ፕሮፖጋንዳዎችን መለየት ፣እንደየ አመጣጣቸው ህጋዊ ፣ሰላማዊና ዴሞክራሲያዊ በሆነ የትግል አግባብ በሃሳባዊ ትግል መመከት ይሮርበታል ፡፡
በአንዳንድ ማህበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎች እየታየ ያለው አደገኛ አዝማምያም ምክንያታዊ ሆኖ የመቅረብ ጉድለት ይታያል ፡፡ መንግስት የዜጎች ደህንነት መጠበቅ አለበት መንግስት ከህዝቡ ጋር በመሆን ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን መስራት አለበት ወንጀል ፈፃሚዎችን በህግ ፊት ቀርበው ተጠያቂ መሆን አለባቸው ብሎ ማንሳት ተገቢ ነው ፡፡ ነውር የለውም ፣የነበረ ፣ያለ እና መኖርም ያለበት ነው ፡፡ መንግስት እያደረገው ያለውም ይሄው ነው ፡፡
በአንፃሩ በሩዋንዳ የተከሰተውን የሁቱሲና ተቱሲ ዓይነት እልቂት እንዲፈጸም የሚቀሰቅሱ የማህበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎችና ብሎጎሮች ግን የጥፋት ሰባኪዎች ናቸው ፡፡ አንዱን ብሄር በሌላው እንዲያምጽ ፋኖ ተሰማራ ፣ክተት ብለው የክተት ጥሩንባ የሚነፉት ሃይሎች እየገናባነው ባለው የፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ፈንጅ እያጠመዱበት መሆናቸውን መውሰድ ይኖርባቸዋል ፡፡ 21ኛው ክፍለ ዘመን ወጣት አለም በግሎባላይዜሽን ህግጋት አንድ መንደር ለመሆን እየተገደደችበት ባለበት ሁኔታና በሃገራችን ደግሞ አንድ የፖለቲካ ኢኮኖሚ ማህበረሰብ ለመገንባት እየተደረገ ባለበት ሁኔታ በሄርን ከብሄር ፣ህዝብን ከህዝብ ለያፋጅ የሚችል ስሜታዊ ቅስቀሳ መቀስቀስ ጠቃሚም ተገቢም አስተማሪም አይደለም ፡፡ የወጣቱ ስራ ጥገኞች የፈፀሙትን ስህተት በስህተት ማረም ሳይሆን ምክንያታዊ በሆነና ዴሞክራሲያዊ የአስተሳሰብ ትግልን በመከተል መታገል ፣ማጋለጥ ወንጀል አድራጊዎችንና እና ተባባሪዎቻቸው የዴሞክራሲያዊ ስርዓታችን ጠባቂ መላእክት በሆነው የተጠያቂነት መርህ እንዲጠየቁ ማድረግ መሆን አለበት ፡፡ ጠባብነትንና ትምክህትን የምንዋጋው በሌላኛው መልክ የጠባብነትና የትምክህተኝነት መንገድ ሳይሆን በአብዮታዊ የዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብ ትግል ነው ፡፡ ጠባብነትና ትምክህት የምንዋጋው አፈ-ሙዝ አንስተን ፋኖ ተሰማራ ብለን ሳይሆን በዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብ ነው ፡፡ ጠባብነትና ትምክህተኝነት ለመዋጋት በህገ-ወጥ መንገድ መታገል ማለት የሚፈልገውን የፀረ-ዴሞክራሲያዊ ብሄርተኝነት አስተሳሰብ ለም መሬት ሆንለት ማለት ነው ፡፡ በመሆኑም ወጣቱ ስሜታዊ ከመሆን ፣በስሜት ከመደግፍና ከመቃወም ወጥቶ በምክንያታዊነት ማመን የምክንያታዊነትን ህግጋት ማክበርና ማስከበር በዚህም የስርዓቱ ነቀርሳ ሆኑትን የጠባብነትና ትምክህተኝነት አመለካከትን በብስለት መታገል ይኖርበታል ፡፡
ክፍል 2 ይቀጥላል ፡፡